ሚያዚያ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በኢትዮጵያ ውስጥ በየጊዜው የሚታየውን የሸቀጦች ዋጋ መናር ለማስቀረት ይረዳል የተባለ የንግድ ድርጅት ለማቋቋም በከፍተኛ እንቅስቃሴ ውስጥ የሚገኘው መንግስት ፣ ድርጅቱ ከተቋቋመ በሁዋላ የማስተዳደር ስራውን ለአሜሪካው የሸቀጦች አከፋፋይ ድርጅት ለማስረከብ በመነጋገር ላይ መሆኑን ፎርቹን ጋዜጣ ዘግቧል። 1 ቢሊዮን ብር የመመስረቻ ካፒታል እንደሚመሰረት የተነገረለት የኢትዮጵያ የሸቀጦች ማከፋፈያ ኢንተርፕራይዝ በሚቀጥለው አመት ስራውን ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል። ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
ሆላንዳዊውን ባለሀብት የደበደቡ 20 ኢትዮጵያውያን በእስር ላይ ናቸው
ሚያዚያ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ሸዋ ዞን በአና ቦራ ወረዳ በማሊማ በሪ ቀበሌ የሚገኘው የሼር ብሌን ኢትዮጵያ የአበባ እርሻ ባለቤት የሆኑት የሚ/ር ባርኖር ልጅ ሚ/ር ጆን የተባሉት ሆላንዳዊው ባለሀብት በሰራተኞች የተደበደቡት ሚያዚያ 7 ሲሆን፣ ድበደባውን ተከትሎ 27 ሰራተኞች ታስረዋል። ከእነዚህ መካከል 7 ሰዎች ከሶስት ሳምንት በላይ ታስረው በዋስ ሲፈቱ 20ዎቹ አሁንም በእስር ላይ ...
Read More »በሊቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ማይታወቁ ስፍራዎች እየተወሰዱ ነው
ሚያዚያ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በተለያዩ እስር ቤቶች የሚገኙ ኢትዮጵያውያኖች እንደገለጹት ከተለያዩ እስር ቤቶች የተውጣጡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ወደ አልታወቁ ስፍራዎች ተሰደዋል። የኢትዮጵያ ዜጎች ከሁሉም ዜጎች ባነሰ ሁኔታ እንደሚስተናገዱ የሚገልጹት እስረኞች ሴቶች ይደፈራሉ፣ ወንዶች ገንዘብ ካላመጡ ይደበደባሉ። ኩሚስ በሚባል እስር ቤት ውስጥ ላለፉት 9 ወራት ታስሮ በስቃይ ላይ የሚገኘው ሽሬ እንደ ስላሴ ተወልዶ ያደገው መምህር ሙሴ ዘ ሚካኤል ...
Read More »የህሊና እስረኞችን ለመጠየቅ ወደ ቃሊቲ የሄዱ ጠያቂዎች በፖሊስ ተባረሩ
ሚያዚያ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- የትንሳኤ በአልን ምክንያት በማድረግ በእስር ላይ የሚገኙትን የህሊና እስረኞች ለመጠየቅ ወደ ቃሊቲ ያመሩት የአንድነት ፓርቲ አመራሮች እስካፍንጫቸው በታጠቁ ልዩ ሀይሎች በግድ ከአካባቢው እንዲርቁ መደረጉን ፍኖተ ነጻነት ዘገበ ወጣቱን ፖለቲከኛና ከፍተኛ አመራር አንዱአለም አራጌና ናትናኤል መኮንን ሽብርተኞች እንደሆኑና በሰላማዊ ትግል ሽፋን ሽብርተኝነትን እንደሚያራምዱ ተደርጎ የቀረበው ሀተታና ውሳኔ እጅግ ያሳዘናቸው በርካታ አመራሮችና አባላቱ ...
Read More »በዜጐች መፈናቀልና እንግልት ላይ ተሣታፊ የሆኑ የመንግስት ሀላፊዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ እንቅስቃሴ ተጀመረ
ሚያዚያ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ የዜጐችን መፈናቀል ለማስቆምና በዜጐች መፈናቀልና እንግልት ላይ ተሣታፊ የሆኑ የመንግስት ሀላፊዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ የሚያግዝ ፒቲሽን ለማስፈረም እየተዘጋጀ መሆኑን አስታወቀ፡፡ ፓርቲው፤ኢትዮጵያዊ ምሁራን የሚሣተፉበትና መፈናቀሉ እያስከተለ ባለው ጉዳት ዙሪያ በመወያየት የመፍትሄ ሀሣብ የሚመነጭበት አገር አቀፍ የፓናል ውይይት እንደሚካሄድም ገልጿል፡፡ አዲስ አድማስ የፓርቲው ን የህዝብ ግንኙነት ሀላፊና የኤዲቶሪያል ቦርድ አባል ...
Read More »በሱዳን በተካሄደው የተኩስ ልውውጥ አንድ ኢትዮጵያዊ ወታደር ተገደለ
ሚያዚያ ፳፰ (ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ደቡብ ሱዳንና ሰሜን ሱዳንን እያወዛገበ ባለው በነዳጅ ዘይት በበለጸገችው የአቤይ ግዛት በማጆክና በሚሴሪያ ጎሳዎች መካከል በተደረገ ጦርነት 20 ሰዎች ሲሞቱ፣ በአካባቢው በሰላም አስከባሪነት የተሰማራ አንድ ኢትዮጵያዊ ወታደር ተገድሎ ሌሎች ሁለት ደግሞ ቆስለዋል። ማጆክ የተባለው ጎሳ ደቡብ ሱዳንን የሚደግፍ ሲሆን ሚሴሪያ ደግሞ ሰሜን ሱዳንን ይደግፋል። በግጭቱ የተገደለው ኢትዮጵያዊ ወታደር ስም አልተገለጸም፣ የኢትዮጵያ ...
Read More »የሸቀጦች ዋጋ የተረጋጋ ቢመስልም አሁንም ከህብረተሰቡ አቅም በላይ ሆነዋል
ሚያዚያ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የትንሳዔ በዓል ገበያ በአዲስ አበባ የተረጋጋ ቢመስልም አሁንም የሸቀጦች ዋጋ በተለይ ከዝቅተኛው ኀብረተሰብ አቅም በላይ መሆኑን በሾላ እና በሳሪስ ገበያ ትላንትና ያሰባሰብናቸው መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ በዚሁ መሰረት የጤፍ ዋጋ ማኛ ከ1850-2000ብር በኩንታል፣ነጭ ጤፍ ከ1750-1800፣ሰርገኛ ከ1600-1700 ዋጋ ይጠየቅበታል፡፡ ቅቤ እንደረጃው ከ180-195 ብር በኪሎ በተለይም ለጋ ቅቤ የሸኖ በኪሎ እስከ 200 ብር ፣ ዶሮ የአበሻ ...
Read More »አንድነት ፓርቲ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች በአፋጣኝ እንዲፈቱ ጠየቀ
ሚያዚያ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ሚያዚያ 24 ቀን 2005 ዓ.ም ይግባኝ ሰሚ ችሎት በእነአንዷለም አራጌ ፍርድ ላይ የሰጠው ውሳኔ ፍ/ቤቶች የገዥው ፓርቲ ጉዳይ አስፈፃሚዎች እንጅ ገለልተኛ ተቋማት አለመሆናቸውን ያሳየ ነው ብሎአል። ፓርቲው “ሽብርተኝነት በናይጀሪያ፣ በአፍጋኒስታን እና በፓኪስታን በእየለቱ የምንሰማው እንጅ የኢትዮጵያ ችግር አይደለም በማለት ገልጾ የከፍተኛው ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ወጣቱን ፖለቲከኛና ከፍተኛ አመራር ...
Read More »ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ የሪፖርተርስ ዊዝአውት ቦርደርስ የ2013 ሽልማት አሸናፊ ሆነ
ሚያዚያ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በስዊድን በስደት ላይ የሚገኘው የቀድሞው የአዲስ ነገር ጋዜጣ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ ሽልማቱን ያገኘው በኢትዮጵያ በሽብረተኝነትና በህገወጥ መንገድ ወደ አገር በመግባት ተከሰው ከአንድ አመት በላይ ታስረው ከተፈቱት የስዊድን ጋዜጠኞች ከሆኑት ማርቲን ሽብየ እና ጆሀን ፒርሰን ጋር በጋራ በመሆን ነው። ጋዜጠኛ መስፍን በውጭ አገር ሆኖ ለፕሬስ ነጻነት በመታገሉ ለሽልማት እንደበቃ ድርጅቱ አስታውቋል። ...
Read More »አለማቀፍ መንግስታት እና ድርጅቶች በእነ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና አንዱአለም አራጌ ላይ የተላለፈውን ውሳኔ አወገዙ
ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በአል በሰላም አደረሳችሁ ሚያዚያ ፳፭ (ሃያ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በወጣቱ ፖለቲከኛ አንዱአለም አራጌ፣ በእውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ በናትኤል መኮንን፣ ክንፈሚካኤል ደበበ ፣ ምትኩ ዳምጤ ፣ ዮሃንስ ተረፈ ፣ ሻምበል የሺዋስ ይሁን አለም እንዲሁም አንዱአለም አያሌው ላይ የስር ፍርድ ቤቱ የሰጠውን ውሳኔ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሚያዚያ 24፣ 2005 ዓም ማጽደቁ አለማቀፍ ...
Read More »