ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ የሪፖርተርስ ዊዝአውት ቦርደርስ የ2013 ሽልማት አሸናፊ ሆነ

ሚያዚያ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በስዊድን በስደት ላይ የሚገኘው የቀድሞው የአዲስ ነገር ጋዜጣ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ ሽልማቱን ያገኘው በኢትዮጵያ በሽብረተኝነትና በህገወጥ መንገድ ወደ አገር በመግባት ተከሰው ከአንድ አመት በላይ ታስረው ከተፈቱት የስዊድን ጋዜጠኞች ከሆኑት ማርቲን ሽብየ እና ጆሀን ፒርሰን ጋር በጋራ በመሆን ነው።

ጋዜጠኛ መስፍን በውጭ አገር ሆኖ ለፕሬስ ነጻነት በመታገሉ ለሽልማት እንደበቃ ድርጅቱ አስታውቋል። ጋዜጠኛ መስፍን “ሽልማቱ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ስራ በመስራት ላይ ላሉ እንዲሁም በእስር ቤት ውስጥ ላሉ የሙያ ባልደረቦቼ እውቅና የሚሰጥ ነው” በማለት ተናግሯል።