.የኢሳት አማርኛ ዜና

በጉዲፈቻ የወሰዱዋቸውን ኢትዮጵያውያን ልጆች የገደሉት አሜሪካውያን ጥፋተኞች ተባሉ

ጳግሜ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ላሪ እና ካሪ ዊሊያምስ የተባሉ አሜሪካውያን ባልና ሚስቶች ሃና ዊሊያምስ የተባለቸውን የ13 አመት ታዳጊ ህጻን፣ ደብድበው፣ አስርበውና አሰቃይተው ገድለዋታል። ግለሰቦቹ በተመሳሳይ መንገድ አንድ ታዳጊ ወጣት በመግደላቸው በአንደኛ ደረጃ የግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለዋል። ባልና ሚስቱ ለታዳጊዎቹ ሞት እርስበርሳቸው በፍርድ ቤት መወቃቀሳቸው ታውቋል። ሁለቱም ግለሰቦች በእድሜ ልክ እስራት ሊቀጡ ይችላሉ ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።

Read More »

የኢትዩጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ፊደራሊዝምን ባላከበረ መልኩ ያለ አግባብ ከክልሎች እንደሚሰበስብ ታወቀ

ጳግሜ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ኤጀንሲ በቴሌቪዥን ቻናል አንድ እና ሁለት የአየር ሰዓት ድልድል ወጥቶላቸው በቀን የአንድ ስዓት ስርጭት የክልሎችን ተደማጭነት እና የልማት ዘገባ ለህዝቡ ለማድረስ ፣ እያንዳንዱ ክልል ለኢቲቪ በአመት አምስት ሚሊየን ብር በነፍስ ወከፍ ይከፍላል፡፡  የኢትዩጵያ ሬዲዩና ቴሌቪዥን በእየአመቱ ከክልሎች ብቻ 55 ሚሊየን ብር ገቢ ያገኛል፡፡ ክልሎች በራሳቸው ሳተለይት ተከራይተው ዝግጀቶቻቸውን ለማቅረብ ጥያቄ ቢያቀርቡም ...

Read More »

በኢትዩጵያ 66 በመቶ የሚሆኑ ቤቶች መፀዳጃ ቤት አልባ ናቸው

ጳግሜ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የማዕከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ የኢትዮጵያ ዌልፌር ሞኒተሪንግ ሰርቬይ ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ በኢትዮጵያ 66 በመቶ የሚሆኑ ቤቶች መፀዳጃ ቤት የላቸውም፡፡ መጸዳጃዎች ካሏቸው ውስጥ 2.2 በመቶ በውኃ የሚለቀቅ፣ 63.8 በመቶ ያህሉ በጉድጓድ የሚጠቀሙ ናቸው፡፡ በሜዳ ወይም በጫካ የሚጠቀሙት 33.7 በመቶ ያህሉን ይሸፍናሉ፡፡ በጫካ ወይም በሜዳ ከሚጠቀሙት 12.5 በመቶ ያህሉ በከተማ ሲሆን 39.5 በመቶው በገጠር አካባቢ ነው፡፡ ወተር ኤይድ ...

Read More »

አንድነት ፓርቲ በአዳማ/ናዝሬት የተሰካ የተቃውሞ ሰልፍ አደረገ

ጳግሜ ፬(አራት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች በተገኙበት ገዢው ፓርቲ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰት ከማውገዝ በተጨማሪ ህዝቡ ለእውነተኛ ለውጥ እንዲነሳ ጥሪ አድርጓል። ሰልፈኛው ሲያሰማቸው ከነበሩት መፈክሮች መካከል ጥያቄያችን ህገመንግስታዊ ነው፣ ውሸት ሰልችቶናል፣ ስራ መግኘት መብታችን ነው፣ ጸረ ሽብር ህጉ በራሱ አሸባሪ ነው፣ መንግስት፣ የኑሮ ድጎማ ያድርግልን፣  ድህነት በወሬ አይጠፋም፣ ርእዮት አለሙ አሸባሪ አይደለችም፣ ...

Read More »

ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ደሳለኝ በኢትዮጵያ ውስጥ አክራሪነት የለም የሚሉ የተቃዋሚ ድርጅቶች አጥፊዎች፣ከሃዲዎች ናቸው አሉ

ጳግሜ ፬(አራት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚኒስትሩ ትላንትና እና ዛሬ ለሕትመት በበቃው ከመንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ላይ እንደተናገሩት “የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በርግጥም ለኢትዮጽያ ሕዝብ ዴሞክራሲ፣መልካም አስተዳደር ልማትና ሠላምን ለማምጣት አጀንዳ አድርገው የሚንቀሳቀሱ ከሆነ አክራሪነትንና ሽብርተኝነትን ከመንግስት ጎን ተሰልፈው ሊያወግዙ ይገባል ብለዋል፡፡ ” በኢትዮጽያ አክራሪነትና ሽብርተኝነት የለም ብለው የሚያስቡ ከሆነ እነዚህ ሰዎች በኢትዮጵያ ውስጥ የሉም ማለት ነው፡፡ በኢትዮጵያ ...

Read More »

የጠ/ሚ ባለቤት በቤተመንግስት ኑሮ መሰላቸታቸውን ገለጹ

ጳግሜ ፬(አራት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቀዳማዊት እመቤት ሮማን ተስፋዬ የቤተመንግስት ኑሮ የሚመች አለመሆኑንና የቀድሞ ጠ/ሚኒስትርንም አኗኗር በማየት ያዝኑ እንደነበር ተናግረዋል። ቀዳማዊት እመቤቷ ትላንት ከወጣው መንግስታዊው ዘመን መጽሔት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ የቤተመንግስት ሕይወት አስደሳች አይደለም ብለዋል፡፡ “ የቤተመንግስትን ሕይወት ለማንም ተመኝቼው አላውቅም፡፡ የሴቶች ጉዳይን ስናቋቁም ስምንት ወር ተመላልሼበታለሁ፡፡ ዛሬ እናንተ ተፈትሻችሁ እንደገባችሁት እኛም ተፈትሸን ነበር የምንገባው፡፡ እዚህ ግቢ ስገባ ወደጠ/ሚኒስትሩ ...

Read More »

አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ በቢሮክራሲው መማረሩን ገለጸ

ጳግሜ ፬(አራት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ታዋቂው አትሌት ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው ቢሮክራሲ የኢንቨስትምንት ስራ  ለመስራት ዋነኛው እንቅፋት መሆኑን ከሪፖርተር ጋር ባደረገው ቃለምልልስ ገልጿል። የመብራትና ውሀና መንገድ ችግሮችን በጋራ መቋቋም ይቻላል ያለው ሀይሌ ፣ ቢሮክራሲው ከፍተኛ ችግር መሆኑን ገለጿል። ሀይሌ እንደሚለው የቢሮክራሲው ዋና ምክንያት በራሳቸው የሚወስኑ ባለስልጣናት መጥፋታቸው ነው። በተለያዩ ሀላፊነት ላይ ያሉ ባለስልጣናት በራሳቸው እንዲወስኑ እስካልተደረገ ድረስ ...

Read More »

የአላሳድ መንግስት የኬሚካል መሳሪያ አለመጠቀሙን አስታወቀ

ጳግሜ ፬(አራት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፕሬዚዳንቱ በህዝቤ ላይ የኬሚካል የጦር መሳሪያ የምጠቀምበት ምንም ምክንያት ለም በማለት ለአንድ የአሜሪካ የቴሌቪዥን ጣቢያ ተናግረዋል። አሜሪካ ሶሪያን ብትደበድብ አንዳንድ ደጋፊ አገሮች አጸፋዊ መልስ ለመስጠት መዘጋጀታቸውንም አላሳድ አክለው ገልጸዋል። ይሁን እንጅ እነዚህን አገሮች  በስም ከመግለጽ ተቆጥበዋል። አለም በሶሪያ ላይ ስለሚወደው የሀይል እርምጃ ተከፋፍሎአል። ፕሬዚዳንት ኦባማ በሶሪያ ላይ እርምጃ ካልተወሰደ ሌሎች አምባገነን መንግስታት ህዝባቸውን በተመሳሳይ ...

Read More »

የጎንደር ህዝብ በአስተዳደሩ መማረሩን ገለጸ

ጳጉሜ ፩(አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከሳምንት በፊት የቀድሞው የኮምኒኬሽን ሚ/ርና የአሁኑ ጠ/ሚ ሀይለማርያም ደሳለኝ አማካሪ አቶ በረከት ስምኦን በመሩት ስብሰባ ላይ ህዝቡ በአስተዳደሩ መማሩን ገልጿል። 50 በመቶ የጎንደር ከተማ ነዋሪ መኖሪያ ቤት የለውም፣ ያሉት አንድ ተናጋሪ ህዝቡ በችግር እየተጠበሰ ስለልማት ቢያወሩት አይገባውም ብለዋል። ህዝቡ መብቱን ሲጠይቅ ተቃዋሚ ነህ እየተባለ እንደሚዘመትበት እኝሁ ግለሰብ አክለው ተናግረዋል። አንድ ሌላ ተናጋሪ ደግሞ አመራሮች ...

Read More »

የዜጎች መፍለስ ለተቃዋሚዎች እየበጀ መሆኑን ኢህአዴግ ገለጸ

ጳጉሜ ፩(አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የግንባሩ ልሳን የሆነው  አዲስ ራእይ እንደገለጸው በህገወጥ መንገድ የሚፈልሱ ሰዎች የመንግስትን ፕሮግራሞች የማይደግፉ ሀይሎችን በመቀላቀል፣ ከጸረ ህዝቦች ጎን እንዲሰለፉ እየተደረጉ በመሆኑ አደጋ ደንቅረዋል። ልሳኑ ” የዜጎች በህገወጥ መንገድ መፍለስ ለፖለቲካ ፍጆታ በር እንደሚከፍት መታሰብ ያለበት ጉዳይ ነው” ካለ በሁዋላ ” በአሁኑ ወቅት በአገራችን እየተገነባ ያለው የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታ መልካም አስተዳደርና ከድህነት ለመውጣት እያደረግን አለነው ...

Read More »