.የኢሳት አማርኛ ዜና

በኦሮሚያ ካሉ ከ2 መቶ በላይ የአበባ ልማት ባለሃብቶች የአካባቢ ተፅዕኖ ግምገማ ማረጋገጫ የወሰዱት ከ10 አይበልጡም ተባለ፡፡

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦሮሚያ የአካባቢ ጥበቃ የአካባቢ ተፅዕኖና ግምገማ መምሪያ ኃላፊ አቶ አሕመድ ሁሴን በኦሮሚያ ክልል አካባቢን ለመጠበቅ እየተደረጉ ስላሉ እንቅስቃሴዎችና አካባቢን በማይጠብቁት ላይ ምን ዓይነት እርምጃ መወሰድ እንዳለበት እንዲሁም ስለተወሰዱ እርምጃዎች እንደገለጹት፣  በኦሮሚያ ክልል ከአካባቢ ተፅዕኖ ጋር የሚነሱ ችግሮች በክልሉ በሚካሄዱ የተለያዩ ፕሮጀክቶች የተነሳ በአካባቢ ላይ ጉዳት ይደርሳሉ፡፡ ይህንን ጉዳት ለመቀነስ አንድ ፕሮጀክት ከመተግበሩ ...

Read More »

ባለፉት ሶስት ኣመታት በሠፈራ ፕሮግራም ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ሕዝብ በአራት ክልሎች እንዲሰባሰብ መደረጉን ከፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ አመለከተ፡፡

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከ2003-2005 ዓ.ም መንግስት መንደር ማሰባሰብ በሚል በሚጠራው የሠፈራ ፕሮግራም በጋምቤላ በ12 ወረዳዎች 38 ሺ፣በቤንሻንጉል ጉሙዝ በ18 ወረዳዎች 77 ሺ ፣በአፋር በ8 ወረዳዎች 10ሺ፣ በሶማሌ በ21 ወረዳዎች 150 ሺ አባወራና እማወራዎች በድምሩ 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ሕዝብ እንዲሰፍር ተደርጓል፡፡ እስከ2007 የትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ዘመን ማጠናቀቂያ ድረስ 85ሺ ቤተሰብ ለማሰባሰብ እየተሰራ ነው ተብሎአል፡፡ በመንደሩ ያልተሰባሰቡ ...

Read More »

የደቡብ ሱዳን መንግስት ቤንቲዩ የምትባለዋን የነዳጅ ከተማ መቆጣጠሩን አስታወቀ

ጥር ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአገሪቱ ጦር ሀይሎች ቃል አቀባይ እንደገለጹት አማጽያኑ የነዳጅ ማውጫ ጉድጓዶች የሚገኙባትን ቤንቲዩን ለቀው የወጡት እኩለ ቀን ላይ ነው። የደቡብ ሱዳን መንግስት አካባቢውን መቆጣጠሩን ቢገልጽም፣ በአማጽያኑ በኩል የተሰጠ ምንም አይነት ምላሽ የለም። መንግስት የነዳጅ ከተማዋን መቆጣጠሩ አማጽያን በመንግስት የቀረበውን ቅድመ ሁኔታ ለመቀበል ይገደዱ ይሆናል የሚል አስተያየቶች ቀርበዋል። በኢትዮጵያ መንግስትና በኢጋድ አባል አገራት ሲደረግ ...

Read More »

ሰማያዊ ፓርቲ ሀሳቡን በኢሳት ላይ ለመግለጽ የማንንም ይሁንታ እንደማይጠይቅ አስታወቀ

ታህሳስ ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ፓርቲው ” የምንናገርበትን የመገናኛ ብዙሃን ማንም እንዲመርጥልን ወይም እንዲወስንልን አንፈቅድም” በሚል ርእስ ባወጣው የአቋም መግለጫ፣ ” ሰማያዊ ፓርቲ መልዕክቱን የሚያስተላልፍበትን መገናኛ ብዙሃን ማንም አካል እንዲመርጥለት ወይም እንዲወስንለት የማይፈልግ መሆኑን ግልፅ ” አድርጓል። “በሕገ መንግስቱ የተረጋገጠውን ማንም ሰው በመረጠው መንገድ ሃሳቡን የማስተላለፍ መብቱን በመጠቀም በኢሳትም ሆነ እድሉን ካገኘ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አቋሙንና እምነቱን ...

Read More »

ከሳውድ አረቢያ የተባረሩ ዜጎች በችግር ላይ መሆናቸው ታወቀ

ታህሳስ ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት ከ150 ሺ በላይ ተመላሽ ዜጎችን ወደ ተወለዱበት ቀየ መልሶ በመላክ በአነስተኛ እና ጥቃቅን በማደራጀት የስራ እድል እንደሚፈጥር ቢያስታውቅም፣ ኢትዮጵያውያኑ ወደ ቀያቸው ከተመለሱ በሁዋላ ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸው ታውቋል። ሰሜን ሸዋ አካባቢ በርካታ ስደተኞች መመለሳቸውን የገለጹት ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ አንድ ሰው፣ ተመላሾቹ በአነስተኛ እና ጥቃቅን ትደራጃላችሁ በሚል ተስፋ ቢመጡም፣ ቃል የተገባላቸው ነገር ባለመፈጸሙ ...

Read More »

ከ20 ቀናት በፊት በድንገት ከኃላፊነታቸው የተነሱት የማዕድን ሚኒስትር ወ/ሮ ስንቅነሽ እጅጉ በምክትላቸው አቶ ቶሎሳ ሻጊ ተተኩ፡፡

ታህሳስ ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርላማው በጠ/ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ፊርማ የቀረበለትን ዕጩ ሚኒስትር አቶ ቶሎሳ ሻጊ ሞቲን ሹመት ተቀብሎ አጽድቆአል፡፡ አቶ ቶሎሳ የማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን በማገልገል ላይ የነበሩ ሲሆን ከማዕድን ጋር ተያያዥ በሆኑ ስራዎች ከ20 ኣመታት በላይ አገልግለዋል፡፡ ከ16 ዓመታት በላይ በማዕድንና ኢነርጂ ሚኒስቴር ውስጥ ከኤክስፐርትነት እስከ ሚኒስትር ዴኤታ ባሉት የኃላፊነት ቦታዎች ሲሰሩ የቆዩትና ...

Read More »

ከ100 ሺ በላይ የሚሆኑ የቴክኒክ እና ሙያ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የብቃት ምዘና ፈተናውን ማለፍ ሳይችሉ ቀሩ

ታህሳስ ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-10ኛ ክፍልን እንዳጠናቀቁ ወደ ዩኒቨርስቲ መግባት ያልቻሉ ታዳጊ ወጣቶች  መሰረተ ልማት ባልተሟላበት ፤ የኮምፒዩተር አቅርቦት በሌለበት ፤ የተሰናዳ የትምህርት ክፍል፣ ወንበር እና የማሰተማሪያ መርጃ መሳሪያዎች ሳይሟሉ እና ከተግባር መሳሪያዎች ጋር በደንብ ሳይተዋወቁ ተምረው ለምረቃ ይበቃሉ፡፡ በየአመቱ ከመቶ ሺህ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች የሚመክኑበት ይህ የትምህርት ዘርፍ አላማው ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት ቢሆንም ውጤታማ ሊሆን ...

Read More »

መቀሌ በውሃ ጥም ውስጥ ናት

ታህሳስ ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የትግራይ ክልል ርዕሰ ከተማ መቀሌ በውሃ ጥም እየተመታች መሆኑዋን ኗሪዎቿ ተናገሩ፡፡ ላለፉት አራት ወራት በሳንምንት አንድ ቀን በወረፋ የምትደረሰው ውሃ ሌሊቱን ሁሉ ስትጠበቅ ታድራለች፣ እንደነዋሪዎች አነጋገር። ከተማ አሰተዳደሩ በበኩሉ ከእርዳታ ድርጅቶች በቂ ገንዘብ በማፈላለግ  በሚቀጥለው አመት የውሃ አቅርቦቱን ለማሻሻል እንሰራለን ብሎአል፡፡ አስተያየት ሰጭዎች በበኩላቸው የዕርዳታ ድርጅቶችን  ከመጠበቅ ለትሃድሶ እያለ ለግብዣ ከሚያወጣው በመቆጠብ ማሰራት እንደሚቻል ...

Read More »

አዋሳ አየር ማረፊያ ሊሰራላት ነው

ታህሳስ ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፋና እንደዘገበው ከተማዋን የሚጎበኙ ቱሪስቶች መጨመራቸውን ተከትሎ በከተማዋ አውሮፕላን ማረፊያ ለማሰራት እድቅ ተይዟል። የኤርፖርቶች ድርጅት የግንባታ መሬት ከአዋሳ መስተዳደር መረከቡን በመግለጽ በአንድ ሚሊዮን ብር የዲዛይን ስራው እንደሚሰራና በአራት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጿል። አዋሳ ከአዲስ አበባ በ270 ኪሜ ርቀት ላይ የምትገኝ ሲሆን በአለፈው የፈረንጆች አመት ከ600 ሺ የአገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ጎብኝተዋታል።

Read More »

አንድነት ፓርቲ ለሚዲያዎች ሃሳብን መግለጽ አሸባሪነት አይደለም አለ

ታህሳስ ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ ባወጣው መግለጫ ሰሞኑን ኢቲቪ ባዘጋጀው ዶክመንተሪ ላይ “መቀመጫውን በውጭ በማድረግ የተለያዩ ዜናዎችንና ፕሮግራሞችን በማሰራጨት የሚታወቀውን ኢሳት(ESAT) ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ጣቢያ ላይ ፓርቲያችን ለአባላቱ እና ለደጋፊዎቹ መልዕክት ማስተላለፉን እንዲሁም እንደፓርቲ ለማንኛውም ሚዲያ የፓርቲያችንን ሰላማዊ እንቅስቃሴ በተመለከተ ስንጠየቅ የመመለስ መብታችንን በሚጋፋ መልኩ የፓርቲያችንን አቋም አዛብቶ ለማቅረብ ሞክሯል” ብሎአል፡፡ ...

Read More »