አዋሳ አየር ማረፊያ ሊሰራላት ነው

ታህሳስ ፴ (ሰላሳ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፋና እንደዘገበው ከተማዋን የሚጎበኙ ቱሪስቶች መጨመራቸውን ተከትሎ በከተማዋ አውሮፕላን ማረፊያ ለማሰራት እድቅ ተይዟል። የኤርፖርቶች ድርጅት የግንባታ መሬት ከአዋሳ መስተዳደር መረከቡን በመግለጽ በአንድ ሚሊዮን ብር የዲዛይን ስራው እንደሚሰራና በአራት ወራት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጿል።

አዋሳ ከአዲስ አበባ በ270 ኪሜ ርቀት ላይ የምትገኝ ሲሆን በአለፈው የፈረንጆች አመት ከ600 ሺ የአገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ጎብኝተዋታል።