.የኢሳት አማርኛ ዜና

የቦስኒያ ክሮሺያ ጄኔራል በችሎቱ ፊት መርዝ ጠጥተው ሕይወታቸውን አጠፉ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 21/2010)በሔግ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የፍርድ ሂደታቸውን ሲከታተሉ የነበሩት የቦስኒያ ክሮሺያ ጄኔራል በችሎቱ ፊት መርዝ ጠጥተው ሕይወታቸውን አጠፉ። በቦስኒያ ሙስሊሞች ላይ በተፈጸመ የጦር ወንጀል ከዚህ በፊት የጥፋተኝነት ውሳኔ የተላለፈባቸውና በ20 አመት እስራት እንዲቀጡ የተፈረደባቸው ጄኔራል አሟሟት ጉዳይ በመጠራት ላይ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ አንድ የቀድሞ የቻይና ጄኔራል በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ምርመራ እየተደረገባቸው ባለበት ወቅት ሕይወታቸውን ማጥፋታቸው ታውቋል። አንድ የቀድሞው ...

Read More »

የጋምቤላ ክልል ለመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ መክፈል አልቻለም ተባለ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 21/2010)በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የኢኮኖሚ ቀውስ እየተባባሰ መቀጠሉ በሚነገርበት በአሁኑ ወቅት የጋምቤላ ክልል ለመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ መክፈል አለመቻሉን ገለጸ። በዚህም በክልሉ የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞች በሙሉ የጥቅምት ወር ደሞዛቸው እስከ ህዳር አጋማሽ እንዳልተከፈላቸው ታውቋል። የጋምቤላ ከተማ ከንቲባ ክልሉ ገንዘብ ለመክፈል ጊዜያዊ ችግር እንዳጋጠመው አረጋግጠዋል። የጋምቤላ ክልል በስሩ የሚያስተዳድራቸው የመንግስት ሰራተኞች በአጠቃላይ 1550 ያህል እንደሆኑ መረጃዎች ያመለክታሉ። ታዲያ እነዚህ ሁሉ ሰራተኞች ...

Read More »

በአማራ ክልል ቻግኒ ከተማ ማንነታቸው ያልታወቀ ሰዎች በፖሊስና በአካባቢው የሚሊሻ ታጣቂዎች ላይ ጥቃት ሰነዘሩ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 21/2010)ይህ በእንዲህ እንዳለ በአማራ ክልል ቻግኒ ከተማ ማንነታቸው ያልታወቀ ሰዎች በፖሊስና በአካባቢው የሚሊሻ ታጣቂዎች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን ለኢሳት የደረሰው መረጃ አመልክቷል። በደቡብ ጎንደር ደጎማም ዛሬ ክፍተኛ የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር ምንጮች ገልጸዋል። በሀዋሳና በአዲስ አበባ አንዳንድ ቦታዎች የትግል ጥሪ ወረቀቶች መበተናቸው ታውቋል። በአዊ ዞን ቻግኒ ከተማ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች በፖሊስና በአካባቢው ሚሊሻ ታጣቂዎች ላይ ጥቃት መሰንዘራቸውን ነው የታወቀው። ...

Read More »

በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ተቃውሞ ተካሄደ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 21/2010)በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ተቃውሞ ተካሄደ። በምስራቅ ሀረርጌ ሰሞኑን የተጀመረው ተቃውሞ ዛሬም የቀጠለ ሲሆን የህወሃት መንግስት ከስልጣን ይውረድ የሚለው ደግሞ ጥያቄያቸው ነው ። በወለጋ የተለያዩ ከተሞች ህዝባዊ ተቃውሞው እንደቀጠለ ነው። በሌላ በኩል በአርባምንጭ ከተማ የሚገኘውን አየር ማረፊያ ሲጠብቁ የነበሩ ወታደሮች መጥፋታቸው ታወቋል። ባህርዳር የሚገኘው የምዕራብ እዝ አየር ምድብ አባላትም ለሁለት ቀናት አድማ አድርገዋል። ዳግም የተቀሰቀሰውንና ለበርካታ ሰዎች መገደል ...

Read More »

ከስልጣን የተወገደው የህወሃት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ራሱን ወደ ጥገኛ ገዢ መደብ የማሸጋገር አዝማሚያ ተጠናውቶት ነበር ተባለ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 21/2010)በአባይ ወልዱ ሲመራ የነበረው የህወሃት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ራሱን ወደ ጥገኛ ገዢ መደብ የማሸጋገር አዝማሚያ ተጠናውቶት እንደነበር የሕወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ በአቋም መግለጫው አስታወቀ። ስራ አስፈጻሚው የውሸት ሪፖርት ሲያወጣ እንደነበርም ተመልክቷል። በትግራይ ማህበረሰብ ዘንድ የአድዋ ተወላጆች ስልጣኑን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጠሩት የሚል አስተያየት በሰፊው በመደመጥ ላይ ነው። ለተራዘሙ ቀናት በመቀሌ ግምገማ ተቀምጦ የነበረው የሕወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ ህዳር 21/2010 ድርጅታዊ የአቋም ...

Read More »

የመውሊድ በአል ተከበረ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር /2010)የነብዩ መሀመድ 1 ሺ 492ኛው የልደት በአል በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ተከብሮ ዋለ። በአሉ በተለይም በኢትዮጵያ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ በድምቀት ተከብሯል። በበአሉ ላይ የእምነቱ ተከታዮች በአሉን ሲያከብሩ የሰላም፣የፍቅርና የመቻቻል አስተምህሮቶችን በመጠበቅ ሊሆን እንደሚገባ ተገልጿል። የነቢዩ መሀመድን አስተምህሮ ህዝበ ሙስሊሙ እርስ በእርሱ በመዋድድና በመረዳዳት ሊተገብረው እንደሚገባ በበአሉ አከባበር ላይ ተገልጿል፡፡ በአሉ በዚህ በአሜሪካም በተለያዩ አካባቢዎች በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ተከብሮ ውሏል።

Read More »

በምስራቅ ሀረርጌ በተለያዩ ከተሞች በተነሳ ተቃውሞ 6 ሰዎች ተገደሉ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 20/2010)በምስራቅ ሀረርጌ በተለያዩ ከተሞች በተነሳ ተቃውሞ 6 ሰዎች ተገደሉ። በአዳማ ናዝሬት ዛሬ በተቀሰቀሰው ግጭት 2 ነዋሪዎች በአጋዚ ሰራዊት መገደላቸው ታወቋል። በምስራቅ ሀረርጌ ጨለንቆ፣ ጉርሱም፣ በደኖና ባቢሌ ህዝባዊ አመጽ ተነስቶ ከመንግስት ታጣቂዎች ጋር ግጭት መፈጠሩንም የደረሰን ዜና ያመለክታል። በአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው እየወጡ ነው። በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ውጥረቱ ተባብሶ መቀጠሉም ታውቋል። የህወሃት ደህንነቶች በኦነግ ስም ወጣቶችን እየመለመሉ በማሰር ላይ ...

Read More »

የሶማሌ ተወላጆችን በቁጥጥር ስር ለማዋል የሶማሌ ክልል ፍቃደኛ አይደለም ተባለ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 20/2010)በኦሮሚያና በሶማሌ ክልል በነበረው ግጭት ተጠርጣሪ የሆኑ የሶማሌ ተወላጆችን በቁጥጥር ስር ለማዋል የሶማሌ ክልል ፍቃደኛ እንዳልሆነ ተገለጸ። በቁጥጥር ስር ለማዋል ተባባሪ ያልሆኑ የሶማሌ ክልል አመራሮች ርምጃ እንዲወሰድባቸው ተወስኗል። በኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች ለወራት በዘለቀውና አሁንም መብረድ ባልቻለው ግጭት የተጠረጠሩ ግለሰቦችን አሳልፎ ለመስጠት ፈቃደኛ ያልሆኑ የሶማሌ ክልል አመራሮች ርምጃ እንዲወሰድባቸው መወሰኑን የዘገበው በሀገር ውስጥ የሚታተመው ሪፖርተር ጋዜጣ ነው። ውሳኔውን ያሳለፈው ...

Read More »

ሼህ መሀመድ አላሙዲንን ጨምሮ ሌሎች የሳውዲ ባለሃብቶችና ልኡላን በዚህ ወር መጨረሻ ሊፈቱ ይችላሉ ተባለ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 20/2010)ትውልደ ኢትዮጵያዊው ሼህ መሀመድ አላሙዲንን ጨምሮ በቁጥጥር ስር የዋሉት የሳውዲ ባለሃብቶችና የልኡላን ቤተሰቦች በዚህ ወር መጨረሻ ሊፈቱ እንደሚችሉ አንድ የሳውዲ ባለስልጣን ገለጹ። ከታሰሩት ውስጥ 95 በመቶው በድርድር ለመውጣት ፈቃደኛ መሆናቸውንም ቢቢሲ በዘገባው አስፍሯል። በድርድሩ መሰረትም የተወሰነውን የሃብታቸውን መጠን ወደ ሳውዲ መንግስት ግምጃ ቤት ማስገባት እንደሚጠበቅባቸውም ተመልክቷል። እጅግ ውድና ዘመናዊ በሆነው ሪትዝ ካርልተን ሆቴል ውስጥ የታሰሩት ባለሃብቶች በቁጥር 201 ...

Read More »

በሊቢያ አፍሪካውያን ስደተኞች እንደሚሸጡ፣እንደሚለወጡና እንደሚገደሉ ታወቀ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 20/2010)በሊቢያ በአንድ ሳምንት ብቻ በመቶዎች የሚቆጠሩ አፍሪካውያን ስደተኞች እንደሚሸጡ፣እንደሚለወጡና እንደሚገደሉ ታወቀ። በመንግስታቱ ድርጅት የፈረንሳይ አምባሳደር እንዲህ አይነቱን ህገወጥ ድርጊት ድርጅቱ ማስቆም አለበት በህገወጥ ድርጊቱ ተሳታፊዎች ላይም ማዕቀብ መጣል አለበት ብለዋል። ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው ጥርስ አልባው የአፍሪካ ህብረት ግን በአቢጃን ኮትድቯር ከአውሮፓ ህብረት ጋር የጋራ ጉባኤ በማካሄድ ላይ ነው። በሊቢያ እየተካሄደ ያለው የባሪያ ንግድ ከሁለት ሳምንት በፊት በሲ ኤን ...

Read More »