.የኢሳት አማርኛ ዜና

በትምህርት ቤት ውስጥ የመንግስትን ፖሊሲዎች በማንሳት ጥያቄዎችን በመጠየቁና ተማሪዎችን ለማነሳሳት ሙከራ አድርጓል በማለት ለአንድ አመት የታሰረው አስቻለው ቢራቱ ተፈታ

ኢሳት ዜና:- ተማሪ አስቻለው በቡታጅራ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሚማርበት ጊዜ ገዢው ፓርቲ ተማሪዎችን ለአባልነት ለመመልመል የሚያደርገውን እንቅስቃሴ በመቃወም፣ እንዲሁም በመሬትና በተዛማጅ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ዙሪያ ጥያቄዎችን በማቅረቡ ተከሶ ለአንድ አመት በእስር እንዲቀጣ ተፈርዶበት ነበር። ተማሪ አስቻለው ለኢሳት እንደገለጠው የገዢው ፓርቲ አባል የሆኑት ርእሰ መምህርና መምህራን አስቻለው የሚያቀርባቸውን ጥአቄዎችም ሆነ ከተማሪዎች ጋር የሚያደርገውን ግንኙነት አይወዱለትም ነበር። በ2002 ዓም ደግሞ ተማሪ አስቻለው ...

Read More »

ኢትዮጵያን ለቀው የሚወጡ ዜጎች ቁጥር በታሪክ ታይቶ በማይታወቅበት ደረጃ ላይ መድረሱ ታወቀ

ኢሳት ዜና:- የኢሳት የባህርዳር ዘጋቢ እንዳለው በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያን በመልቀቅ ወደ የመንና ሱዳን የሚሰደደው ህዝብ በእጅጉ አስደንጋጭ ሆኗል። የአማራ ክልል የተለያዩ ወረዳዎች ባለስልጣናት ያቀረቡትን ሪፖርት ተንተርሶ በላከው ዘገባ ተሰዳጆቹ የከተማ ነዋረዎች ብቻ ሳይሆኑ ገበሬዎች ጭምር ናቸው። በደቡብ ጎንደር በየሳምንቱ ከ250 እስከ 300፣ በሰሜን ወሎ ከ300 እስከ 450 ፣ በደቡብ ወሎ ከ200 እስከ 300፣ በጎጃም ከ400 እስከ 550 የሚደርሱ ገበሬዎችና የከተማ ...

Read More »

በኢትዮጵያ የሽብርተኝነት ክስ የተመሰረተባቸው ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞች፤ ዐቃቤ ህግ ባቀረበባቸው የመጀመሪያ ምስክር ቃል መሳቃቸውን ቢቢሲ ዘገበ

ኢሳት ዜና:- እንደ ቢቢሲ ዘገባ፤ ዐቃቤ ህግ በጋዜጠኞቹ ላይ የመጀመሪያው የአቃቤ ህግ ምስክር ኢንስፔክተር መሀመድ አህመድ የተባለ የፖሊስ አባል ነው። ኢንስፔክተር መሀመድ፤ ጆሀን ፐርሰን እና ማርቲን ሽብዬ የተባሉት ሁለቱ የስዊድን ጋዜጠኞች የኦጋዴ ብሔራዊ ነፃነት ግንባር ተዋጊዎችን የሚያሰለጥኑ ናቸው  በማለት ነው የመሰከረው። የኢንስፔክተሩ ምስክርነት ከተሰማ በሁዋላ ፍርድ ቤቱ ጋዜጠኞቹን ፦የኦጋዴ ብሔራዊ ነፃነት ግንባር ተዋጊዎችን ስለመርዳትና ስለማሰልጠን በተሰማው ምስክር ላይ ያላቸውን አስተያዬት ...

Read More »

የኢህአዴግ መንግስት የሙስሊሙን ማህበረሰብ ከሁለት መክፈሉንና አክራሪ ያላቸውን ወገኖች በማሳደድ ላይ መሆኑን ሙስሊሞች ተናገሩ

ኢሳት ዜና:- የኢሳት ዘጋቢ ያነጋገራቸው ሙስሊሞች እንዳሉት በአሁኑ ጊዜ መንግስት አንዱን ወገን አህባሽ ሌላውን ወገን ደግሞ ዋህቢ በማለት መከፋፈሉ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ቅሬታን ፈጥሯል። ክፍፍሉን ተከትሎም በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ለእስር ተዳርገዋል። በአዲስ ዘመን ከተማ ደግሞ የወረዳው የእስልምና ሀላፊ የነበሩት በታጣቂዎች መገደላቸው ታውቋል። መንግስት በፖሊሲ ደረጃ ቀርጾና በ10 ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ መድቦ የሙስሊሙ ማህበረሰብ አህባሽን ...

Read More »

በደቡብ ክልል በዳውሮ ዞን የዋካ ከተማና አካባቢው ህዝብ ከመብት ጥያቄዎች ጋር ያነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ ከ90 በላይ ሰዎች መታሰራቸው ተሰማ ችግሩ ግን አሁንም አልበረደም

ኢሳት ዜና:-ከሳምንት በፊት  በዋካ ከተማ ከወረዳና ከልማት ጋር በተያያዘ የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ የመንግስት ባለስልጣናት ችግሩን ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ለመፍታት ከመሞከር  ይልቅ የሀይል አማራጭ ተጠቅመዋል። በዚህም የተነሳ በየቀበሌው የሚገኙ ወጣቶች መንግስትን ለመገልበጥ አስባችሁዋል እየተባሉ ከእየቤታቸው እየተወሰዱ በመታሰር ላይ ናቸው። በርካታ ወጣቶችም እስሩን በመሸሽ አካባቢያቸውን ለቀው እየወጡ ነው። መመህራን እና ተማሪዎች ባደረጉት ስብሰባ ደግሞ የመንግስት ባለስልጣናት የወሰዱትን እርምጃ አውግዘዋል። ተማሪዎቹና መምህራኑ የመብት ...

Read More »

የቀድሞው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ፕሬዚዳንት የነበሩት የአቶ ያረጋል አይሸሹም ንብረት በፍርድ ቤት ታገደ

ኢሳት ዜና:-በአቶ ያረጋል አይሸሹምና በህወሀት ባለስልጣናት መካከል የተነሳውን የፖለቲካ ውዝግብ ተከትሎ በሙስና የተከሰሱት አቶ ያረጋል የእርሳቸውና የባለቤታቸው ንብረት እንዲታገድ ፍርድ ቤት ትእዛዝ አስተላልፏል። ፍርድ ቤቱ፣ አቶ ያረጋል በባለቤታቸው ፣ በልጆቻቸውና በእርሳቸው ስም ተመዝግበው የሚገኙ በአሶሳ በ1200 ስኩየር መሬት ላይ የሰፈረ የግል መኖሪያ ቤት፣ በዚሁ ከተማ የሚገኝ 1000 ካሬ ሜትር ቦታ፣ በቦሌ አካባቢ የሚገኘው 500 ካሬ መሬት፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ የሚገኝ 4132 ...

Read More »

በየመን በስደት ላይ የምትገኝ ኢትዮጵያዊት ህጻን በሞት ሽረት ትግል ውስጥ እንደምትገኝ ተገለጠ

ኢሳት ዜና:-ህጻን ሀያት መስከረም 12/2000 ዓ.ም በእቅፍ ነው ስደት የወጣችው። ገና የአንድ አመት ልጅ እያለች ነው በባህር ወደ የመን ከመጡት እናቷ እና አባቷ ጋር አብራ የመጣችው። ድንገት ማንም ሰው በዚህ እድሜው ከሚያየው ስቃይ በላይ ስቃይን አጣጥማለች። እናቷ በሞት የተለየቻት ይህች ህጻን እንዳዛሬው 5 ዓመት ሞልቷት መሳቅ መጫወት ሳትጀምር፣ ርሀብ ጥሟን መናገር ሳትችል፣ ህመሜ እዚህ ጋር ነው በማትልበት ወቅት የ 11 ...

Read More »

ኢሳት በሳተላይት የ24 ሰዓት ሬዲዮ ስርጭት ጀመረ (የኢሳት ጋዜጣዊ መግለጫ)

  የኢትዮጵያ ሳተላየት ቴሌቪዥን (ኢሳት) ጥቅምት 20 ቀን 2004 ዓም ኢሳት የ24 ሰዓት የሳተላይት ራዲዮ ስርጭት ማስተላለፍ መጀመሩን በተመለከተ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የኢትዮጵያ ሳተላየት ቴሌቪዥን (ኢሳት) የሰተላይት ራዲዮ በቀጥታ ወደ ኢትዮጵያ ማስተላለፍ መጀመሩን ለህዝብ ሲያሳውቅ በታላቅ ደስታ ነው። ኢሳት የሳተላይት ራዲዮ ስርጭት የጀመረበት ዋና ምክንያት ለኢትዮጵያ ህዝብ ለዴሞክራሲና ለነጻነት ለሚያደርገው ትግል ህዝብ ትክክለኛ መረጃ በማቅረብ ትግሉን ለማገዝ የገባውን ቃል አጠናክሮ ...

Read More »

አንድ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁር፣ ጋዜጠኛ ዮናስ በላይ እና ሦስት የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች የፍትህ ስርዓቱንና አቶ መለስ በፓርላማ ያደረጉትን ንግግር ተቹ

ኢሳት ዜና:- ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ  ምሁር፤አንድ  ዳኛ ህገ-መንግስቱ  ውስጥ በተቀመጠው  መሰረት  የዳኝነት ነፃነቱን  እንዴት ያለ ተፅዕኖ ሊገብር ይችላል?” የሚለውን ጉዳይ ለማየት፤ “ዻኛው ማነው?”፣ዳኛ ለመሆን የሚያስችሉት መስፈርቶችስ ምንድናቸው? የሚለውን የኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ማየት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል። የዴሞክራሲ ሥርዓት በሚከተሉ  አገሮች የዳኝነት አካል ሲዋቀር  ዜጐች  በተለያየ  መንገድ እንደሚሳተፉ፤ በዳኝነት  የሚሾሙት  ሰዎችም ዕድሜያቸው በሰል  ያለና  ከፍተኛ  ልምድ ያካበቱ  መሆናቸውን  የሚናገሩት እኚሁ ምሁር፣ ኢትዮጵያ ...

Read More »

መንግስት በአዲስ አበባ የታየውን ከፍተኛ የስንድ እጥረት ለመቅረፍ ከውጭ አገር የገዛውን ስንዴ ለህብረተሰቡ ማከፋፈል ሊጀምር መሆኑ ታወቀ

ኢሳት ዜና:-በቅርቡ በአዲስ አበባ የታየውን ከፍተኛ የስንዴ እጥረት ተከትሎ የዳቦ መጠን መቀነሱን እንዲሁም ህብረተሰቡ ዳቦ ለማግኘት ረጅም ሰአት ተስለፎ መጠበቅ ግድ ብሎት እንደነበር መዘገባችን ይታወቃል። ይህን ተከትሎ መንግስት ከዚህ ቀደም ዘይት ለማከፋፈል እንደሞከረው ሁሉ ስንዴም ለነዋሪው በዚህ ሳምንት ውስጥ ማከፋፈል እንደሚጀመር ታውቋል።  አንድ ቤተሰብ በነፍስ ወከፍ የሚገዛው  የስንዴ መጠን ባይታወቅም፣ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ግን ከ25 እስከ 50 ኪሎ ሊደርስ ይችላል። ግብርናው ...

Read More »