ደቡብ ሱዳን በእርስ በርስ ግጭት እየታመሰች ነው

ታህሳስ ፱(ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :-በፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር እና በቀድሞው ምክትላቸው ሪክ ማቻር መካከል የተነሳው ውዝግብ የዲንቃና የኑዌር ጎሳዎችን እርስ በርስ እንዲዋጉ እያደረጋቸው መምጣቱን ዘገባዎች ያመለክታሉ። የሪክ ማቻር ደጋፊዎች ጆንግሌ አካባቢ የሚገኙ የተለያዩ ቦታዎችን መቆጣጠራቸው ተሰምቷል። ምንም እንኳ የአገሪቱ መሪ መፈንቅለ መንግስቱን ማክሸፋቸውን ቢናገሩም፣ በሌሎች አገሪቱ ክፍሎች አሁንም ውጊያዎች እየተካሄዱ ነው። ከስልጣን የተባረሩት ሪካ ማቻር ፕሬዚዳንት ሳል ቫኪር ስልጣን ...

Read More »

የአለማቀፉ ፍርድ ቤት በኬንያው መሪ ላይ የጀመረውን ምርመራ አቋረጠ

ታህሳስ ፱(ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :-ዋና አቃቢ ህጓ ምርመራውን ለማቋረጥ የተገደዱት ሁለቱ ዋና ምስክሮችን ለማግኘት ባለመቻላቸው ነው። ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ከ6 አመት በፊት በተነሳውና ከ1 ሺ 200 በላይ ሰዎች የተገደሉበትን የምርጫ ማግስት ረብሻ አነሳስተዋል በሚል ነው። በምክትላቸው ዊሊያም ሩቶ ላይ የተጀመረው ክስ ይቀጠል አይቀጥል የታወቀ ነገር የለም። የአፍሪካ መሪዎች ክሱ እንዲቋረጥ ሲወተውቱ ቆይተዋል። ፕሬዚዳንቱ ክሱን እየተከታተሉ አገሪቱን ለመምራት አይችሉም ...

Read More »

የጌዲዮ ዞን የሀገር ሽማግሌዎች በረሀብ መጠቃታቸውን የሚያመለክት ደብዳቤ ተፈራርመው ለዞኑ መስተዳድር አቀረቡ

ታህሳስ ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :-በጌዲዮ ዞን በሚገኙ 9 ወረዳዎች ውስጥ በዚህ ወር ውስጥ ባልተለመደ ሁኔታ ከፍተኛ ረሀብ በመከሰቱ የዞኑ የአገር ሽማግሌዎች ህዝቡ ያለበትን አሳሳቢ ሁኔታ በመግለጽ የተፈራረሙበትን ደብዳቤ ዛሬ ለዞኑ መስተዳድር አስገብተዋል። በከፍተኛ ደረጃ ተደናገጡት የዞኑ ባለስልጣናት መረጃው ይፋ እንዳይወጣ ለማድረግ ዛሬ ቀኑን ሙሉ በስብሰባ ተወጥረው መዋላቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። የአገር ሽማግሌዎቹ  የገጠሩ ህብረተሰብ በከፍተኛ ሁኔታ በመራቡ መንግስት ...

Read More »

የግንቦት7 ህዝባዊ ሀይል “መጪው አመት ህዝብን የመታደግ እርምጃ የሚወሰድበት አመት ይሆናል” አለ

ታህሳስ ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :-ህዝባዊ ሀይሉ የተመሰረተበትን አንደኛ አመት በማስመልከት ባወጣው መግለጫ ” ያለፈው አንድ አመት የመሰባሰብ ድርጅት መሰረታዊ የሆኑ የፖለቲካና የወታደራዊ ስልጠና የተሰጠበት፣ የድርጅት ማጠናከሪያና የማጥራት ሂደት የተካሄደበት ” ነበር ብሎአል። መጪውን አመት የተለየ የሚያደርገው ህዝባዊ ሀይሉ በህዝብ ላይ በሚደርሰው ግፍና ውርደት ከሚሰማው ከፍተኛ ብስጭትና ቁጭት አልፎ ባለፈው አመት ሊደርስላቸው ያልቻለውን የአገራችንን ግፉአን ህዝቦች መታደግ የሚችልበትን እርምጃዎች ...

Read More »

የቆዳ ፋብሪካዎች የጥሬ ቆዳና ሌጦ አቅርቦት ችግር ገጥሞናል አሉ።

ታህሳስ ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :-በአሁኑ ወቅት በሃገራችን ያሉት የቆዳ ፋብሪካዎች የግብዓት ፍላጎታቸው በዓመት ከ40 ሚሊዮን በላይ የበግና ፍየል ሌጦና ከ2 ሚሊየን በላይ የበሬ ቆዳ ሲሆን፥ እየቀረበላቸው ያለው የቆዳ መጠን  ከ16 እስክ 17 ሚሊየን ሌጦ እና በቆዳ ደግሞ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በታች ነው። ከዚህ በመነሳት ሃገሪቱ ከዘርፉ የምትጠብቀውን ገቢ ማሳካት አስቸጋሪ እንደሆነ ነው የኢትዮጵያ ቆዳ ኢንዱስትሪ ልማት ኢንስትቲዩት ...

Read More »

በደቡብ ሱዳን የመፈንቅለ-መንግስት ሙከራ አልተደረገም ሲሉ የፕሬዚዳንቱ ተቃዋሚ ተናገሩ

ታህሳስ ፰(ስምንት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :-ሪክ ማቻር ከተደበቁበት ቦታ ሆነው ለአለማቀፍ የመገናኛ ብዙሀን እንደገለጹት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ተቃዋሚዎቻቸውን ለመምታት የተጠቀሙበት ዘዴ ነው ብለዋል። የፕሬዚዳንቱ ጠባቂዎች እርስበርሳቸው መጋጨታቸውን የገለጹት የቀድሞው ምክትል ፕሬዚዳንት ማቻር፣ ይሁን እንጅ የሳልቫኪር መንግስት አጋጣሚውን ተጠቅሞ ተቀናቃኞችን እያሰረ ነው ሲል አክለዋል። በአገሪቱ ውስጥ የሚታየው ውጥረት በማየሉ አዲሲቷ አፍሪካዊት አገር በእርስበርስ የጎሳ ጦርነት ትታመሳለች ተብሎ ይፈራል። ሪክ ማቻር ያሉበት ቦታ ...

Read More »

በኢትዮጵያ በዲያስፖራው ከተያዙ 744 ፕሮጀክቶች ውስጥ ሩቡ እንኳን በአግባቡ ተግባራዊ አልሆኑም ተባለ፡፡

ታህሳስ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :-ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የዳያስፖራ ተሳትፎ ጉዳዮች ዳሬክቶሬት ጀኔራል የተገኘ መረጃ  በግምት ከ2-3 ሚሊዮን የሚደርሱ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በተለያዩ የአለም ከፍሎች ቢኖሩም ለአገራቸው ያላቸው አስተዋጽኦ ግን አነስተኛ ነው ብሎአል። አውሮፖና አሜሪካ የኢትዮጵያውያኑ ዳያስፖራዎች ዋነኛ መዳረሻዎች ሲሆኑ በርካታ የዳያስፖራው አባላትም በእነዚሁ አህጉራት ይገኛሉ ይላል። እውቅና ያገኙ ተመራማሪዎች ፤ የጤና ባለሙያዎች ፤የዩንቨርስቲ መምህራን ፤በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ...

Read More »

ለሚቀጥሉት ሶስት አመታት ለመንግስት ሰራተኛው የሚጨመር ደሞዝ አይኖርም ተባለ

ታህሳስ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :-የመንግስት ሰራተኛው በከፍተኛ የኑሮ ውድነት እየተሰቃዩ መሆኑን እንደሚያዉቁ የተናገሩት ሁለት የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣኖች፣ ይሁን እንጅ በሚቀጥሉት ሶስትና አራት አመታት በጉልህ የሚታይ ደሞዝ ጭማሪ እንደማይኖር ገልጸዋል። በየአምስት አመቱ የቤተሰብ ፍጆታቸው በተመረጡ ናሙናዎች ተወስዶ በሚለካው የግሽበት አሃዝ ስሌት መንግስት የኑሮ ውድነቱ በአንድ አሃዝ መውረዱን ቢገልጽም፣ የኑሮ ውድነት ግን አለመርገቡን ነዋሪዎች ይናገራሉ። የማእከላዊ ስታትስቲክስ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ...

Read More »

በአዲስአበባ አስተዳደር የተጠያቂነት ችግርን በመፍራት ውሳኔዎችን ማስተላለፍ አልተቻለም ተባለ

ታህሳስ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :-በተለይ ከመሬት ይዞታ ጋር በተያያዘ ውሳኔ የሚያስፈልጋቸውና በታችኛው አመራር ጭምር ሊፈቱ የሚገቡ ጉዳዮች ተጠያቂነትን ከመፍራት አኳያ ወደ መካከለኛና ከፍተኛ አመራሩ የመግፋት ጉዳይ በተደጋጋሚ መከሰቱ አሳሳቢ መሆኑ ሰሞኑን በተደረገው ግምገማ ላይ ቀርቧል፡፡ አስተዳደሩ የ2006 የመጀመሪው ሩብ ዓመት የስራ አፈጻጸም  በገመገመበት መድረክ ላይ ተጠያቂነትን ለመሸሽ ሲባል ስራዎችን ወደላኛው አካል የመግፋት ጉዳይ በበጀቱ ኣመቱ አሳሳቢ ችግር ሆኖ ...

Read More »

በደቡብ ሱዳን ግጭቱ አልበረደም

ታህሳስ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም  ኢሳት ዜና :-ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ተሞክሮ የነበረው መፈንቅለ መንግስት መክሸፉን በተናገሩ ማግስት ግጭት መነሳቱን ረዩተርስ ዘግቧል። አልፎ አልፎ ይሰማ የነበረው ተኩስ በተከታታይ መሰማቱን የገለጸው ረዩተርስ፣ የአሜሪካ ልዩ ልኡክ የሆኑት ዶናልድ ቡዝ ሁኔታው ውጥረት የበዛበትና ያልተረጋጋ መሆኑን ገልጸዋል። እስካሁን ባለው መረጃ 26 ሰዎች እንደተገደሉ ቢታወቅም አንዳንድ የመገናኛ ብዙሀን ከ60 በላይ ወታደሮች እንደተገደሉ እየዘቡ ነው። ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር የቀድሞው ምክትላቸው ስልጣን ...

Read More »