በአብርሃ ጅራ ከተማ በቁጥጥር ስር የዋሉት የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሃለፊ በህዝብ ግፊት ተለቀቁ

ነሃሴ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምእራብ አርማጭሆ ዞን በአብርሃ ጅራ ከተማ ነዋሪ የሆነው የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ወጣት አባይ ዘውዱ ዛሬ ሰኞ ጠዋት በአካባቢው ከሚገኘው የመከላከያ ካምፕ በመጡ መቶአለቃ ተስፋየ ስዩምና መቶ አለቃ ቅባቱ  ተዋጅ በተባሉ የመከላከያ  የመረጃ እና የደህንነት ሰራተኞች ከታሰረ በሁዋላ የአካባቢው ህዝብ ባደረገው ጫና ለመፈታት ችሎአል። ወጣት አባይ በኤርትራ ከሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ጋር በራዲዮ ግንኙነት ...

Read More »

የደቡብ ጎንደር የመኢአድ ዋና ጸሃፊ ባልታወቁ ሰዎች ታፍነው ተወሰዱ

ነሃሴ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመኢአድ የሰሜን ጎንደር የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ የሆኑት አቶ ዘመነ ምህረት ለኢሳት እንደገለጹት የደቡብ ጎንደር ዋና ጸሃፊ አቶ ጥላሁን አድማሴ ባለፈው ቅዳሜ 8 ሰአት ላይ በ6 ፌደራል ፖሊሶች ታፍኖ መወሰዱን ገልጸዋል። ፖሊሶቹ መሳሪያ አለው በሚል ፍትሻ አድርገው የነበረ ቢሆንም ምንም አለመገኘታቸውንና አቶ ጥላሁንን ወዳልታወቀ ቦታ መውሰዳቸውን  አቶ ዘመኑ ገልጸዋል። በሰሜን እና ደቡብ ጎንደር እየደረሰ ...

Read More »

ኦህዴድ በየደረጃው ያሉ አመራሪዎችን ለአስቸኳይ ስብሰባ ጠራ

ነሃሴ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሁሉም የኦሮምያ ክልሎች  በሚገኙ ዞኖች ውስጥ የሚገኙ አስተዳዳሪዎች፣ የግብርና ዋና እና ምክትል ሃላፊዎች፣ የሴቶች ጽ/ቤት ፣ መሬት ጥበቃ ፣ ሲቪል ሰርቪስ እና መልካም አስተዳደር ፣ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ፣ ውሃና ማእድን፣ ገጠር መንገድ ፣ ጥቃቅንና አነስተኛ ጽ/ቤት ፣ ገንዘብና ኢኮኖሚ ፣  ትምህርት/ጽ/ቤት፣ እና  የወጣቶችና ስፖርት ሃላፊዎች ከነገ ጀምሮ ለአስቸኳይ ስብሰባ እንዲከቱ ተደርጓል። አስቸኳይ ስበሰባው ...

Read More »

የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች ራሳቸውን እያገለሉ ነው

ነሃሴ ፲፱(አስራ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኮንዶምኒየም ቤቶች በወቅቱ ዕጣ ወጥቶ ለሕብረሰቡ ማስተላለፍ ካለመቻሉ ጋር ተያይዞ ቆጣቢዎች በመሰላቸትና ተስፋ በመቁረጥ ከፕሮግራሙ ራሳቸውን እያገለሉ መሆኑ ተሰምቷል። የአዲስአበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ዋና ስራአስኪያጅ አቶ መስፍን መንግሥቱ ሰዎች በተለያየ ምክንያት እየለቀቁ መሆኑን አምነው ነገር ግን ከተስፋ መቀረጥ ጋር እንደማይገናኝ ለመንግሥት መገናኝ ብዙሃን አረጋግጠዋል፡፡ እንደእሳቸው ገለጻ በድጋሚ ከተመዘገቡ 993ሺህ የኮንዶምኒየም ፈላጊዎች መካከል 7ሺ ...

Read More »

የጠ/ሚንስትር ጽ/ቤት በሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት ዙሪያ አስቸኳይ ስብሰባ አካሄደ

ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ኢህአዴግ ምንጮች እንደገለጹት በሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት አብዲ ሙሃመድ ኡመር እና በክልሉ የካቢኔ አባሎች መካከል የተፈጠረውን ልዩነት ተከትሎ በጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ጽ/ቤት በተካሄደው አስቸኳይ ግምገማ ፣ ፕሬዚዳንቱ ፈጸሟቸው የተባሉ በርካታ ወንጀሎች ተዘርዝረው ቀርበዋል። አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በሰብሳቢነት በመሩት ግምገማ ላይ ም/ል ጠ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የጠ/ሚኒስትሩ የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊ አለቃ ጸጋየ በርሄ፣ የደህንነት ...

Read More »

በባቲ ኦሮሞዎች እና የአጎራባች አፋር ክልል ነዋሪዎች ግጭቱ ተባብሶ መቀጠሉ ተሰማ

ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በባቲ ወረዳ ልዩ ስሙ ቡርቃ በተባለ ቀበሌ አካባቢ የሚኖሩ የሁለቱ አጎራባች ክልሎች ነዋሪዎች በተለያዩ ጊዜያት በተኩስ እየተጋጩ በሁለቱም ወገን ሰዎች እየሞቱ ቢሆንም ፤የሁለቱ ክልል መሪዎች ጉዳዩን ለመፍታት ምንም ዓይነት ጥረት አለማድረጋቸው እንዳሳዘናቸው የባቲ ከተማ ነዋሪዎች ገልጸዋል፡፡ በቡርቃ  ቀበሌ  የተቀበረ ወርቅ አለ ተብሎ መነገሩ ለግጭቱ መባባስ ምክንያት መሆኑን የሚናገሩት የአይን እማኞች፣ የኦሮምያ ዞን መሬቱን ...

Read More »

የዋጋ ንረቱ አለመረጋጋት ከፍተኛ አመራሩን ውጥረት ውስጥ ከቷል

ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከሐምሌ ወር ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ደመወዝ ጭማሪ መደረጉ ከተነገረ  በኃላ ይበልጥ የተባባሰውንየዋጋንረትለማስታገስመንግሥትእየወሰዳቸውያሉትየሃይልእርምጃዎችውጤትባለማምጣታቸውከፍተኛአመራሩውጥረትውስጥ ከመወደቁጋርተያይዞአምራች፣አስመጪናአከፋፋይነጋዴዎችዋጋአለመጨመራቸውንለሕዝብእንዲናገሩ እየተገደዱ ነው። በሰኔ ወር አጋማሽ የሲቪል ሰርቪስ ቀን ሲከበር ከአንድ ዓመት በላይ ተጠንቶ የዋጋ ንረት በማያስከትል መልኩ የደመወዝ ጭማሪ መደረጉ በጠ/ሚኒስትርኃ/ማርያምደሳለኝከተነገረበሃላበዋናነትበሸቀጦች፣በምግብናበቤትኪራይዋጋላይከፍተኛንረትመከሰቱየመንግሥትን ጭማሪ ዋጋቢስነት ያሳየ ከመሆኑም በላይተ አማኒነቱንም ጎድቶአል፡፡ በተለይየጭማሪውመጠንእጅግዘግይቶሲነገርገዥውፓርቲበራሱአባሎችናደጋፊዎችጭምርእየተተቸመምጣቱከፍተኛአመራሩንአደናግጦአል፡፡በዚህም መደናገጥ በየመንደሩየሚገኙተራሱቆችንከማሸግናነጋዴዎችን ከማሰርጀምሮበራዲዮናበቴሌቪዥንነጋዴውንየማጥላላትናየማስፈራራትስራዎችንሲያከናውንየቆየቢሆንም የዋጋንረቱአሁንምቢሆንሊረጋጋአልቻለም። የንግድ ሚኒስቴር ከደመወዝ ጭማሪው በፊት ዋጋ ጨምረው የነበሩ ...

Read More »

የወልድያ ከተማ ህዝብ ብሶቱን አሰማ

ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የብአዴን ከፍተኛ ሹሞች ከከተማው ህዝብ ተወካዮች፣ ከኢህአዴግ አባላትና ከተለያዩ የመስሪያ ቤት ሃላፊዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ነዋሪዎች የተለያዩ ችግሮችን አንስተዋል። አንድ አስተያየት ሰጪ የጤና ተቋማት መድሃኒት በማጣታቸው አግልግሎት እየሰጡ አለመሆኑን ተናግረዋል ሌላ አስተያየት ሰጪ ደግሞ የመብራት ችግር የከተማው ችግር መሆኑን ገልጸዋል ኮብልስቶን ለይስሙላ ተብሎ የሚሰራ በመሆኑ ለህዝቡ ችግር እየፈጠረ መሆኑን አንድ ሴት አስተያየት ሰጪ ...

Read More »

የባህር ዳር ጊዮን ሆቴል ባለቤት በ7 አመት እስራት ተቀጡ

ነሃሴ ፲፮(አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በባህርዳር ከተማ ነዋሪ የሆኑት የአቶ መለስ ዜናዊ የቅርብ ዘመድ አቶ ወልዱ ወልደአረጋይ በ7 አመትፅኑ እስራት መቀጣታቸውን የክልሉ ዘጋቢያችን ገልጻለች። መንግስት ማግኘ ትየነበረባትን ከ900 መቶ ሺህ ብር በላይ እንዳያገኝ ያደረገ ታክሰ በማጭበርበር ወንጀል የተከሰሰው ወልዱና ቤተሰቡ ኃላፊነት የተወሰነየግል ማህበርበእስራትናበገንዘብእንዲቀጣየምዕራ ጎጃም ዞንየባህርዳርምድብችሎትውሳኔማስተላለፉንየአማራክልልጠቅላይፍርድቤትየውሳኔመዛግብትዋቢ በማድረግ ገልጻለች። የምዕራብጎጃምፍርድቤትባህርዳርምድብችሎት  ወልዱናቤተሰቡሀላፊነቱየተወሰነየግልማህበር፣ አቶ ወልዱወልደአረጋይ እና አቶብስራትወልዱወልዳረጋይየተጨማሪእሴትታክስሰብስቦያለማሳወቅናያለመክፈልእንዲሁምየተጨማሪእሴትታክስባልሆነደረሰኝግብይትበማካሔድወንጀል በአመትስድስትነጥብሶስትሚልዩንብርመሰብሰባቸው ተጠቅሷል፡፡ ከዚህምለመንግስትመግባትየነበረበትከስድስትመቶሺብርበላይለግልጥቀማቸውአውለዋል ብሎአል። ተከሳሽወልዱወልዳረጋይበ7 አመትፅኑእስራትእንዲቀጡአንደኛተከሳሽወልዱናቤተሰቡሀላፊነቱየግልማህበርንበተመለከተበህገ-ሰውነትየተሰጠውድርጅትበመሆኑ ...

Read More »

ኢህአዴግ አክራሪነትን ለመዋጋት አዲስ ስታራቴጂ መንደፉን አስታወቀ

ነሃሴ ፲፭(አስራ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በእስልምና በኦርቶዶክስና በፕሮቴስታንት ሃይማኖቶች እየታየ ያለው የአክራሪነት አደጋ ለስርዓቱ ፈተኝ ሆኗል በሚል አላማ የተሰናዳው አዲስ ስትራቴጂ በአማራ፣ በኦሮምያና በደቡብ ክልሎች ከመጪው አመት ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል። በሰነዱ ዙሪያ  ላይ የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ የዞን እና ለአክራሪነት ተጋላጭ ናቸው የተባሉ የአንዳንድ ወረዳ አመራሮች እንዲሁም የሚመለከታቸው የተለያዩ መስሪያ ቤት አመራሮች ውይይት አድርገውበታል። ውይይቱን የተካፈሉት የክልሉ ከፍተኛ ...

Read More »