የፌደራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ብቃቴ አድጓል አለ

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌዴራል ፖሊስ በ2006 በጀት ዓመት በ36 መዝገቦች በኦነግ፣ በግንቦት ሰባት፣ በኦብነግ፣ በጋህነን፣ በቤህነን እንዲሁም በአልሻባብ ተጠርጥረው የተያዙ ሰዎችን መክሰሱን በመጥቀስ የፌደራል ፖሊስ ሽብርን የመከላከል አቅሙ እንዳደገ በመግለጽ ራሱን አሞካሽቷል፡፡ ፌዴራል ፖሊስ ለመንግስት መገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ ባለፈው ዓመት 36 የሽብር መዝገቦች መካከል በ27 ቱ ላይ ምርመራ ተጠናቆ ለሚመለከተው ክፍል መመራቱን አስታውቆአል፡፡ ከነዚህ ...

Read More »

በሸኮ መዠንገርና በዞን አስተዳዳሪዎች መካከል ንግግር እየተደረገ ነው

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የአካባቢው ወኪል እንደገለጸው በሸኮ መዠንገር ተወካዮችና በከፋ፣ ሸካ፣ ጋምቤላና ቤንች የዞን አመራሮች መካከል በሃይማኖት አባቶች አማካኝነት በቴፒ ውይይት እያደረጉ ነው። የአካባቢው ባለስልጣናትን በማናገር እንደዘገበው የንግግሩ ዋና አላማ ሸሽተው በየጫካው ውስጥ የሚገኙ የመዠንገርና የሸኮ ተወላጆች አሳምኖ ወደ ቀያቸው ለመመለስ ነው። ይሁን እንጅ ለድርድር የሄዱ አንዳንድ የመዠንገር ተወላጆች መታሰራቸው ንግግሩን ተአማኒነት አሳጥቶታል። አሁንም ...

Read More »

የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘጠኝ የኢትዮጵያ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጥቅምት 11/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት የትብብር ስምምነት መፈራረማቸውን ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል። ፓርቲዎቹ ነጻ አሳታፊና ታአማኒ ምርጫ እንዲካሄድ በትብብር ለመስራት፣ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋትና የዜጎችን ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ በጋራ ለመታገል መስማማታቸውን ትብብር ሰነዱ ላይ አስፍረዋል። ትብብሩን እንዲመሩ  ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ከሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር፣ አቶ ኤርጫፎ ኤርጌሎ ከከንባታ ...

Read More »

በሃረሪ የሚታየው የስኳር እጥረት መባባሱን ነዋሪዎች ገለጹ

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወኪላችን እንደሚለው በከተማው የታየውን የስኳር እጥረት ተከትሎ፣ አንድ ኪሎ ስኳር እስከ 30 ብር በመሸጥ ላይ ነው። በተመሳሳይ መልኩ የሚታየው የዘይት እጥረት  የነዋሪውን ኑሮ አስከፊ እንዳደረገው ገልጿል። የስኳር እጥረቱ በደቡብ፣ በኦሮምያና በአማራ አካባቢዎችም በስፋት እየታየ ነው። መንግስት የስኳር ፋብሪካዎች ወደ ምርት ሲገቡ ስኳር ወደ ውጭ መላክ እንችላለን በማለት ህዝቡን ለማረጋጋት ቢሞክርም፣ የተባሉት ፋብሪካዎች ...

Read More »

በአማራ ክልል የመምህራንና ሰራተኞች ፍልሰት ጨምሯል

ጥቅምት ፲፩(አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በክልሉ በሚገኙ የሰሜን ጎንደር ጠረፋማ ወረዳዎች፣ በአዊ፣ በዋግ ህምራ እና በኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞኖች የሚገኙ መምህራን ወደ አጎራባች ክልሎች  በመፍለሳቸው  በትምህርቱ ጥራት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እያደረሰ መሆኑን  ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡ ክፍተቱን ለመሸፈን አስረኛ ክፍል ያጠናቀቁ እና በልዩ ልዩ ሙያ የተመረቁ ተማሪዎች እንዲቀጥሩ ለአራቱ ዞኖች ደብዳቤ  ስለደረሳቸው ይህንኑም እየተፈጸሙ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የሚቀጠሩ አዲስ መምህራን ...

Read More »

ኢንሳ በኢሳትና ሌሎች ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እንዲወስድ ተጠየቀ

ጥቅምት ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ሰሞኑን አሻሽሎ ያዘጋጀውና የኢህአዴግ ምክር ቤት አባላት እንዲወያዩበት የተዘጋጀው  ሰነድ ለኢሳት የደረሰ ሲሆን፣ ሰነዱ የመንግስት የመረጃና የደህንነት መስሪያ ቤት ወይም ኢንሳ በኢሳት በአሜሪካ እና በጀርመን ድምጾች ላይ እርምጃ እንዲወስድ ከመማጸን ጀምሮ መንግስት በሴቶች፣ በወጣቶችና በምሁራን ስም የሃይማኖት ማህበራትን እንዲቋቋሙ እገዛ እንዲደርግ፣ በሰርተፍኬትና በዲግሪ ደረጃ የሃይማኖት ትምህርት የሚሰጡ ተቋማት እንዲቋቋሙ እገዛ ...

Read More »

ኢህአዴግ በምርጫው ዙሪያ የ20 በ80 እቅዱን ተግባራዊ እያደረገ ነው

ጥቅምት ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመንግስት የኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ሬድዋን ሁሴን በተመራውና ሁሉም የክልል መንግስታት የኮሚኒኬሽንና የመገናኛ ብዙሃኖች የተሳተፉበት የኢህአዴግ የምርጫ ዘመቻ ፕሮፓጋንዳ ዝግጅት ባለፈው ቅዳሜ ሲጠናቀቅ ሁሉም የክልል ሚዲያዎች ቀጣዩን ምርጫ ሊያሳምን የሚችል አቀራረብ ፣ ዜና እና ፕሮግራም እንዲየቀርቡ እንዲሁም በምርጫው የኢህአዴግ አሸናፊት ቅኝት ውስጥ ስራዎችን እንዲሰሩ ታዘዋል። ብአዴን በምርጫው ዙሪያ ለከፍተኛ አመራሩ የሰጠውን ስልጠና ወደ መካከለኛ አመራሩ ...

Read More »

የመከላከያ ሰራዊት አባላት በህዝቡ ላይ የሚወስዱትን እርምጃ ነዋሪዎች በሰልፍ ተቃወሙ

ጥቅምት ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምእራብ አርማጭሆ የመከላከያ ሰራዊትን የሚከዱ ወታደሮችን ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ፣ በአካባቢው የሚገኙት ወታደሮች በህዝቡ ላይ የአጸፋ እርምጃ እየወሰዱ ነው። የምእራብ አርማጭሆ ወረዳ ነዋሪዎች እሁድ እለት የተቃውሞ ሰልፍ ያደረጉ ሲሆን፣ ለአሁኑ ሰልፍ ምክንያት የሆነው ጥቅምት 7 አንድ ወታደር መጥፋቱን ተከትሎ የአጎቱ ልጅ የሆነ የጤና ባለሙያ ከፍተኛ ድብደባ ደርሶበት እንዲታሰር ከተደረገ በሁዋላ ነው። በቅርቡ አንድ የሚሊሻ ...

Read More »

በኤርትራ ድንበር ይጠብቁ የነበሩ ወታደሮች በመረጃ ስህተት ሲተኩሱ ዋሉ

ጥቅምት ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት በኤርትራ ድንበር አካባቢ በጥበቃ ላይ የሚገኙ ወታደሮች በመረጃ ስህተት ለ33 ዲቃዎች በባዶ ሜዳ ላይ ሲተኩሱ የዋሉ ሲሆን፣ ለጦሩ የተሳሳተ መረጃ በመስጠት መከላከያን አወናብደዋል የተባሉ 5 ወታደሮች ተይዘው እንዲታሰሩ ተደርጓል። ከግንቦት ሰባት ተኩስ ተከፈተ ተብሎ ለማዕከላዊ የጦር ሃይል ሪፖርት የተደረገ ሲሆን ይህን ተከትሎ ከፍተኛ መደናገጥ ተገብቶ እንደነበር ከኢህአዴግ የፖለቲካና የደህንነት ምንጮች ...

Read More »

ከሚኒስትሮች ውጭ ያሉ ሁሉ በፖለቲካ ስብሰባዎች ላይ ሞባይል መያዝ እንደሌለባቸው አቶ በረከት ተናገሩ

ጥቅምት ፲(አስር) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አቶ በረከት ስምኦን ” የኢሳት ዘጋቢዎችን መቆጣጠር አልተቻለም፣ በውስጣችን ያሉ ሃይሎች ጣሉን” ያሉ ሲሆን፣ ከሚኒስትሮች በስተቀር የደህንነት ሃይሎችም ሆኑ ጋዜጠኞች በፖለቲካ ስብሰባ ላይ ሞባይል ይዘው እንዳይገቡ እንደከለከሉ ትእዛዝ አስተላልፈዋል። አቶ በረከት ከዚህ ቀደም እርሳቸውንና ድርጅታቸውን የተመለከቱ መረጃዎች በኢሳት ተደጋግሞ መውጣት እንዳበሳጫው የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። የኢህአዴግን ምክር ቤት ስብሰባዎች ለመዘገብ የተጠሩ ጋዜጠኞችና ስብሰባውን እንዲከታተሉ ...

Read More »