የኤሌክትሪክ ታሪፍ መጨመር የዋጋ ንረት ማስከተሉ አይቀርም ተባለ

ኢሳት (ጥቅምት 24 2008) የኢትዮጵያ መንግስት ኤለክትሪክ አገልግሎት ታሪፍን ከ 50 በመቶ በላይ ለመጨመር መወሰኑ ከተጠቃሚው ህዝብና ባለሀብቶች ተቃውሞ እንደገጠመው ተገለጠ። አገልግሎቱ ለበርካታ አመታት በመንግስት ድጎማ መቆየቱን የገለጸው የኢትዮጵያ ኤለክትሪክ ሀይል መስሪያ ቤት በበኩሉ በአሁኑ ወቅት ቢያንስ ወጪውን የሚሸፍን ታሪፍ በማስፈለጉ 50 በመቶና ከዚያም በላይ ሊደርስ የሚችል ጭማሪ በቅርቡ ተግባራዊ እንደሚደረግ ይፋ አድርጓል። በኤሌክትሪክ አገልግሎት መቆራረጥ ለአመታት ያህል ቅሬታቸውን ሲያቀርቡ ...

Read More »

የአቶ ፋንታሁን ልጅና አንድ የሰማያዊ የምክር ቤት አባል በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ

ጥቅምት ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአንድነት መግባባትና መተባበር ሊቀመንበር የሆኑት የአቶ ፈንታሁን ብርሃኑ የ13 አመት ሴት ልጅ በአንድ ወጣት በስለት በአሰቃቂ ሁኔታ ስትገደል፣ ሌላው የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት አባል አቶ አበራ ሃይለማርያምም በዚሁ ወጣት ተገድለዋል። አቶ ፋንታሁን ለኢሳት እንደተናገሩት ጎረቤታቸው የሆኑት አቶ አበራ የተገደሉት ምናልባትም ጩኸት ሰምተው ልጃቸውን ለመታደግ በመሞከራቸው ሳይሆን አይቀርም። ወጣቱ ግድያውን የፈጸመው ትናንት ...

Read More »

ብአዴን የተነሳበትን አቅጣጫ መሳቱ ተነገረ፡፡

ጥቅምት ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ብአዴን በአሁኑ ጊዜ የደረሰበት ደረጃ ሁሉንም ነገር በዘመድ አዝማድ የሚሰራበት የተሳሳተ አቅጣጫ የተከተለበት ሁኔታ ላይ መድረሱን ነባር ታጋዮች ተናገሩ፡፡ ከመጀመሪያዎቹ የትግል ዓመታት ጀምረው እስከ ድሉ ማግስት ድረስ ለድርጅታቸው ታማኝ በመሆን የአካልና የህይወት መስዋዕትነት የከፈሉ የቀድሞ ታጋዮች እንደተናገሩት ፤በስርዓቱ ከጥቃቅን ነገሮች ጀምሮ እሰከ ከፍተኛ ደረጃ ያሉ ጉዳዮች ካለሙስና የማይሰራበት ደረጃ መድረሱ እንዳሳዘናቸው ...

Read More »

በጅጅጋ የንግድ ቤቶች ተቃጠሉ

ጥቅምት ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ታይዋን በሚባለው አካባቢ ይሰሩ የነበሩ ነጋዴዎች፣ ሆን ተብሎ በተቀሰቀሰ እሳት ድርጅታቸው እስከ ሙሉ ንብረታቸው እንደወደመባቸው ለኢሳት ተናግረዋል። ድርጊቱ ከሌሊቱ 11 ሰአት ላይ የተፈጸመ ሲሆን፣ መንግስት በአካባቢው ለሚያሰራው መንገድ ድርጅቶችን በማቃጠል ካሳ እንዳይከፍል ለማድረግ ነው በማለት ነዋሪዎች ተናግረዋል። በቃጠሎው ከ15 በላይ የንግድ ድርጅቶች የወደሙ ሲሆን፣ ፖሊሶች ህዝቡ እሳቱን እንዳያጠፋ ሲከላከሉ ታይቷል። ይህም ...

Read More »

የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ እግርኳስ ቡድን በፌዴሬሽኑ ችግር ከአፍሪካ ዋንጫ ውድድሩ ውጪ ሆኑ

ጥቅምት ፳፬ (ሃያ አራት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-እንደ አውሮፓዊያን ዘመን አቆጣጠር በ2016 ዓ.ም በመጪው አመት ህዳር ወር ላይ በካሜሮን አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአፍሪካ የእንስቶች የእግርኳስ ዋንጫ ላይ ለመሳተፍ የሚያስችለውን የእጣ ድልድል ላይ ለመሳተፍ የሚያስችለውን የተሳትፎ ማረጋገጫ ደብዳቤ የኢትዮጵያ እግርኳስ ማኅበር በወቅቱ ባለመላኩ ምክንያት የአፍሪካ እግርኳስ ማኅበር የኢትዮጵያ ሴቶች እግርኳስ ቡድን ሉሲዎችን ከምድብ ድልድል እጣ ውጪ መሆናቸውን አስታውቋል። የአፍሪካ እግርኳስ ...

Read More »

በባህርዳር የተደረገውን የባጃጆች አድማ ተከትሎ ሹፈሮች እየታሰሩና የገንዘብ ቅጣት እንዲከፍሉ እየተደረገ ነው

ጥቅምት ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዘጋቢያችን ነዋሪዎችን በማነጋገር እንደገለጸው፣ በአድማው የተሳተፉትን ሹፌሮችን ወደ እስር ቤት የወሰዱ ሲሆን፣ ከፖሊስ የሚደርስባቸውን ጫና በመፍራት ስራ እንጀምራለን ያሉት ደግሞ 500 ብር ቅጣት ካልከፈሉ እንደማይጀምሩ ተነግሯቸዋል። ከፖሊስ የሚደርሰውን ወከባ በመፍራት ብዙ ሹፈሮች አሁንም ራሳቸውን ደብቀዋል። አንድ የባጃጅ ባለሃብት መንግስት ለምን አድማ አደረጋችሁ በሚል እየተበቀለ ነው ብለዋል።

Read More »

በኢትዮጵያ ድርቁ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ

ጥቅምት ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በፓስፊክ ውቅያኖስ መሞቅ ሳቢያ የሚከሰተው በኤሊኖ የአየር መዛባት ተከትሎ ከሰሃራ በታች ባሉት አገራት በተከሰተው ድርቅ ሳቢያ በተለይ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ሕጻናት ከፍተኛ በሆነ የምግብ እጥረት ሰለባ እንደሆኑና የዕርዳታ ለጋሽ አገሮች እርዳታውን በአፋጣኝ ካልሰጡ አደጋው የከፋ ሊሆን እንደሚችል ሰኞ እለት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ። በአስር ዓመት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ አሰቃቂ ችጋር በኢትዮጵያ ...

Read More »

በአርሲ በቆጂ ከተማ አንድ ባለሃብት የተቃዋሚ ዳጋፊ ናቸው በሚል ድርጅታቸው ተዘጋ

ጥቅምት ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት የአካባቢው ወኪሎች እንደገለጹት ባለሀብቱ አቡ ታዬ የሚባለውን ሆቴላቸውን ጨምሮ 3 ሱፐር ማርኬቶች ( የገበያ ማእከሎች)፣ 6 የእቃ ማጠራቀሚያ መጋዚኖች፣ እና ሌሎች በርካታ ድርጅቶቻቸው ታሽገውባቸዋል። ባለሀብቱ ገዢውን ፓርቲ አይደግፉም በሚል ከዚህ ቀደም ከፍተኛ ግብር ሲጣልባቸው ቆይቷል። ተቃዋሚዎችን መደገፉን ትተህ ኦህዴድን ደግፍ እየተባሉ ቢዋከቡም፣ ባለሃብቱ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል። ችግራቸውን የሚሰማላቸው በማጣታቸው አዲስ ...

Read More »

ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ከዛንቢያ ወደ ኢትዮጵያ ተላኩ

ጥቅምት ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዛንቢያ መንግስት በሕገወጥ መንገድ ወደ አገሬ ገብተዋል በማለት ይዞ አስሮ ያቆያቸውን ስደተኞች ወደየአገራቸው መመለሱን ያስታወቀ ሲሆን ከእነዚህ ተመላሽ ስደተኞች ውስጥ ሰባቱ ኢትዮጵያዊያን መሆናቸውንና ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመግባት በመሸጋገሪያነት በዛንቢያ ለማቋረጥ ሲሞክሩ በጸጥታ ኃይሎች ተይዘው መታሰራቸው ተገልጿል። የቅጣት ጊዜያቸውን አጠናቀዋል ያላቸውን 7 ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ 2 ሶማሊያዊያን፣ 3 ቡሩንዲዊያን፣ 4 ታንዛኒያዊያን እና 3 ...

Read More »

አብዬ የሚገኙት የሱዳን ወታደሮች ተመድ በዶላር ካልፈላቸው የስራ ማቆም አድማ እንደሚያደርጉ አስጠነቀቁ።

ጥቅምት ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-250 የሚሆኑት የሱዳን የተመድ የሰላም አስከባሪ አባላት፣ በአገሪቱ ያለው የዋጋ ንረት ህይወታቸውን ለመምራት ስላላስቻላቸው ፣ ተመድ በአገሪቱ ገንዘብ ከሚከፍላቸው በቀጥታ በዶላር እንዲከፈላቸው ጠይቀዋል። በሱዳን የሰፈሩት የተመድ የሰራዊት አባላት አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን ናቸው። ኢትዮጵያውያን ወታደሮች ወርሃዊ ክፍያቸውን የሚያገኙት በብር ቢሆንም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቅሬታ ሲያቀርቡ አይሰማም። ከ10 አመት በፊት ድርጅቱ የሚከፍለን ገንዘብ በቀጥታ ...

Read More »