Amsterdam

በሞያሌ ከተማ ዛሬም ግድያ አለመቆሙን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ

በሞያሌ ከተማ ዛሬም ግድያ አለመቆሙን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ (ኢሳት ዜና ማጋቢት 03 ቀን 2010 ዓ/ም) ባለፈው ቅዳሜ በሞያሌ ከተማ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከ13 ሰዎች በላይ መግደላቸውን ተከትሎ ግድያውና ውጥረቱ አሁንም ድረስ ያለ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ትናንት ምሽት አንድ የኮንሶ ብሄረሰብ ተወላጅ ሌሊት ላይ በ10 ጥይቶች ተደብድቦ ተገድሎአል። አንድ የምዕራብ ጉጂ አካባቢ ተወላጅ የሆነ ወጣት ደግሞ በ 2 ጥይቶች ተመትቶ ቆስሏል። ...

Read More »

በርካታ ባለስልጣናት ሰዎችን በመኪና ገጭተው ቢገድሉም እስካሁን ለፍርድ አልቀረቡም

በርካታ ባለስልጣናት ሰዎችን በመኪና ገጭተው ቢገድሉም እስካሁን ለፍርድ አልቀረቡም (ኢሳት ዜና ማጋቢት 03 ቀን 2010 ዓ/ም) የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት የአገዛዙ ባለስልጣናት ሰዎችን በመኪና እየገጩ ቢገድሉም እስከዛሬ ግን ለፍርድ ቀርበው ሲቀጡ አልታዬም። ወብሸት ገብረ-እግዚአብሄር የተባለው የኢህአዴግ ወጣቶች ሊግ መስራችና የአዲስ አበባ ወጣቶች ሊግ ሰብሳቢ የነበረና በልደታና ቂርቆስ ክፍለ ከተሞች ኢህአዴግ ጽ/ቤት ሃላፊ አንድ በድህነት ውስጥ የሚገኙ እናት በመኪና ገጭቶ ቢገድልም ፣ ...

Read More »

አዲ ረመጥ በሚገኘው ሱር ኮንስትራክሽን ላይ የቦንብ ጥቃት ተፈጸመ

አዲ ረመጥ በሚገኘው ሱር ኮንስትራክሽን ላይ የቦንብ ጥቃት ተፈጸመ (ኢሳት ዜና ማጋቢት 03 ቀን 2010 ዓ/ም) የአካባቢው ምንጮች በፎቶ ግራፍ አስደግፈው በላኩልን መረጃ ባለፈው አርብ አዲ ረመጥ ላይ በሚገኘውና የህወሃት ንብረት በሆነው ሱር ኮንትስራክሽ ኩባንያ ንብረት ላይ ከሌሊቱ 7 ሰዓት ላይ የቦንብ ጥቃት ተፈጽሞ በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል። ጥቃቱ የደረሰው የሱር አማካሪ በሆነው ልደት ኮንሳልታንት የግል ድርጅት ላይ መሆኑን የአካባቢው ...

Read More »

በነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ መዝገብ የተከሰሱት ተከሳሾች “ ትገደላላችሁ” የሚል ዛቻ እንደደረሰባቸው ተናገሩ

በነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ መዝገብ የተከሰሱት ተከሳሾች “ ትገደላላችሁ” የሚል ዛቻ እንደደረሰባቸው ተናገሩ (ኢሳት ዜና ማጋቢት 03 ቀን 2010 ዓ/ም) ችሎቱ የተሰየመው በአቃቢ ህግ ምስክር ላይ ብይን ለመስጠት የነበረ ቢሆንም፣ “ባለው የስራ ሂደትና መዝገቡ ሰፊ ስለሆነ፣ ለዛሬ ሊደርስልን አልቻለም፣ ስለሆነም ለመጨረሻ ግዜ አንድ ቀጠሮ መስጠት ግድ ሆኖብናል” በማለት መሃል ዳኛው ተናግረዋል። ጠበቆች “እስረኞቹ ያሉበትን ሁኔታ ግንዛቤ ውስጥ አስገብታችሁ አጭር ...

Read More »

ከድንበር ማካለል ጋር በተያያዘ ጋብ ብሎ የሰነበተው የኮሬና የጉጂ ማህበረሰብ ግጭት እንደገና አገረሸ

ከድንበር ማካለል ጋር በተያያዘ ጋብ ብሎ የሰነበተው የኮሬና የጉጂ ማህበረሰብ ግጭት እንደገና አገረሸ (ኢሳት ዜና የካቲት 30 ቀን 2010 ዓ/ም) ለሳምንታት ጋብ ብሎ የሰነበተዉና በአካባቢው የአገዛዙ ካድሬዎች አማካኝነት መለኮሱን ነዋሪዎች የሚናገሩት የኮሬና ጉጂ ኦሮሞ ማህበረሰብ ግጭት እንደገና በማገርሸቱ፣ የዜጎች ህይወት ማለፉን የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። ለግጭቱ ማገርሸት አሁንም የአካባቢዉ ህብረተሰብ አገዛዙን ተጠያቂ አድርጓል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ከለላ በማድረግ የሁለቱ ክልሎች ...

Read More »

በአዲስ አበባ ከ2500 በላይ የሚሆኑ ቤቶችን የማፍረስ ዘመቻ ተጀመረ

በአዲስ አበባ ከ2500 በላይ የሚሆኑ ቤቶችን የማፍረስ ዘመቻ ተጀመረ (ኢሳት ዜና የካቲት 30 ቀን 2010 ዓ/ም) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተገን በማድረግ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ልዩ ስሙ ኪዳነ ምህረት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ቤት ሰርተው ይኖሩ የነበሩ ከ2500 በላይ አባዎራዎችና እማዎራዎች፣ ቤታቸው በላያቸው ላይ እንዲፈርስባቸው ተደርጓል። ፈረሳውን ተከትሎ በአማካኝ ከ12 ሺ ያላነሱ ሰዎች ቤት አልባ ይሆናሉ። በመላው አገሪቱ ...

Read More »

ቤት ፈላጊዎች ለኮንዶሚኒየም ግንባታ በሚል ያጠራቀሙትን ገንዘብ በብዛት ማውጣት መጀመራቸው ስጋት ላይ የገባው አገዛዙ ሚኒስትሩ ይቅርታ እንዲጠይቁ ሊያደርግ ነው

ቤት ፈላጊዎች ለኮንዶሚኒየም ግንባታ በሚል ያጠራቀሙትን ገንዘብ በብዛት ማውጣት መጀመራቸው ስጋት ላይ የገባው አገዛዙ ሚኒስትሩ ይቅርታ እንዲጠይቁ ሊያደርግ ነው (ኢሳት ዜና የካቲት 30 ቀን 2010 ዓ/ም) ሪፖርተር ጋዜጣ በቅርቡ በርካታ የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች ቁጠባቸውን እያቋረጡ ነው በሚል የሰራው ዘገባ የአገዛዙ ባለስልጣናትን በእጅጉ አስቆጥቷል። ጋዜጣው ከ900 ሺ ዜጎች በላይ ቤት ፈላጊዎች የባንክ አካውንት ከፍተው ቁጠባ ቢጀምሩም፣ 624 ሺ ተመዝጋቢዎች ቁጠባ ማቆማቸውን የከተማ ...

Read More »

ባለፈው ሳምንት የተደረገውን የስራ ማቆም አድማ ተሳትፋችሁዋል የተባሉ የህሊና ምግብ ፋብሪካ ሰራተኞች ቅዳሜና እሁድ ያለ ክፍያ እንዲሰሩ ታዘዙ

ባለፈው ሳምንት የተደረገውን የስራ ማቆም አድማ ተሳትፋችሁዋል የተባሉ የህሊና ምግብ ፋብሪካ ሰራተኞች ቅዳሜና እሁድ ያለ ክፍያ እንዲሰሩ ታዘዙ (ኢሳት ዜና የካቲት 30 ቀን 2010 ዓ/ም) ለገጣፎ የሚገኘው ህሊና የተመጣጠነ ምግብ አምራች ኩባንያ ባወጣው ማስጠንቀቂያ ሰራተኞች ያለ ምንም ክፍያ ቅዳሜ እና እሁድ እየገቡ የማካካሻ ስራ እንዲሰሩ ታዘዋል። ድርርጅት ከዚህ በሁዋላ ሰራተኞች በስራ ማቆም አድማ የሚሳተፉ ከሆነ ያለ ምንም እረፍት ከ4-5 ወራት ...

Read More »

አቶ ኤርሚያስ ጠቅል አመልጋ በህወሃቱ ኮሎኔል አብረሃ የግድያ ዛቻ እንደደረሰባቸው አጋለጡ

አቶ ኤርሚያስ ጠቅል አመልጋ በህወሃቱ ኮሎኔል አብረሃ የግድያ ዛቻ እንደደረሰባቸው አጋለጡ (ኢሳት ዜና የካቲት 30 ቀን 2010 ዓ/ም) ከሚኖሩበት ሰሜን አሜሪካ ወደ አገራቸው በመግባት ከአገዛዙ ባለስልጣናት ጋር ምንም ዓይነት ንክኪ ሳይኖራቸው ኢትዮጵያ ውስጥ መዋእለ ንዋያቸውን በማፍሰስ በግሉ የንግድ ዘርፍ ከተሰማሩ በጣት ከሚቆጠሩ ባለሃብቶች አንዱ የሆኑት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ፣ ድርጅታቸው ሆን ተብሎ በተቀነባበረ ሴራ ኪሳራ ላይ እንዲገባ መደረጉን ከሸገር ኤፍኤም ሬዲዮ ...

Read More »

ራሱን ኮማንድ ፖስት ብሎ የሚጠራው ቡድን በኦሮምያ ክልል አመራሮች ላይ እርምጃ እየወሰደ ነው

ራሱን ኮማንድ ፖስት ብሎ የሚጠራው ቡድን በኦሮምያ ክልል አመራሮች ላይ እርምጃ እየወሰደ ነው (ኢሳት ዜና የካቲት 29 ቀን 2010 ዓ/ም) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ሰበብ በማድረግ ራሱን ኮማንድ ፖስት ብሎ የሚጠራው ቡድን በኦሮምያ ክልል ፖሊሶችና አመራሮች ላይ የሚወስደውን እርምጃ ቀጥሎበታል። እርምጃው በኦህዴድ ላይ ከፍተኛ አደጋ ደቅኖበታል። በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ በተለይን በለገጣፎ አካባቢ ተመድበው ይሰሩ የነበሩ የኦሮምያ ፖሊስ አባላት ምሽት ላይ ...

Read More »