በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዝርፊያ እየተፈጸመባቸው ነው (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 17 ቀን 2010 ዓ/ም) ኢትዮጵያኑ እንዳሉት የአገሪቱ ዜጎች የፖለቲካ ተቃውሟቸውን ለመግለጽ ወደ አደባባይ ከወጡ በሁዋላ የስደተኞችን ንብረቶች በመዝረፍ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል። ኢሳት ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን እንደገለጹት፣ በዝርፊያው በርካታ ኢትዮጵያውያን ሃብትና ንብረታቸውን አጥተዋል። በሌላ በኩል ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው 26 ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ሞዛንቢክ ውስጥ ተያዙ በሕገወጥ መንገድ ሞዛምቢክን አቆራርጠው ወደ ደቡብ አፍሪካ ...
Read More »Amsterdam
በሽንሌ ዞን ተቃውሞው እንደቀጠለ ነው
በሽንሌ ዞን ተቃውሞው እንደቀጠለ ነው (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 16 ቀን 2010 ዓ/ም) በሶማሊ ክልል በሽንሌ ዞን የተጀመረው ህዝባዊ የለውጥ እንቅስቃሴ ዛሬም ቀጥሎ ውሎአል። ባርባርታ የሚል ስያሜ የተሰጣቸው ወጣቶች የአብዲ አሊን አገዛዝ በመቃወም የተለያዩ የመብት ጥያቄዎችን በመጠየቅ ላይ ሲሆኑ ፣ ሃድሃጋላ በሚባለው አካባቢ የክልሉ ልዩ ሃይል በነዋሪዎች ላይ ተኩስ መክፈቱ ታውቋል። በተኩስ ልውውጡ ምን ያክል ሰዎች እንደተጎዱ የታወቀ ነገር የለም። ትምህርት ...
Read More »ከ 8 ሚሊዮን ያላነሱ ኢትዮጵያዊያን አፋጣኝ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ሲል ተመድ አሳሰበ
ከ 8 ሚሊዮን ያላነሱ ኢትዮጵያዊያን አፋጣኝ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ሲል ተመድ አሳሰበ (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 16 ቀን 2010 ዓ/ም) በመላው ኢትዮጵያ በተከሰተ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ምክንያት ከ 8 ሚሊዮን ያላነሱ ዜጎች አፋጣኝ የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ። ከአፋጣኝ እርዳታ ፈላጊ ዜጎች ውስጥ 1.8 ሚሊዮን የሚሆኑ የርሃብ ተጠቂዎች በሶማሊያ ክልል ውስጥ የሚገኙ ዜጎች ሕይወታቸውን ለማዳን አፋጣኝ የምግብ እርዳታ ይገባቸዋል ሲል ተመድ ...
Read More »የደራሲ ይስማእከ ወርቁን ሕይወት ለመታደግ ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በባሕርዳር ከተማ ሊዘጋጅ ነው
የደራሲ ይስማእከ ወርቁን ሕይወት ለመታደግ ልዩ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በባሕርዳር ከተማ ሊዘጋጅ ነው (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 16 ቀን 2010 ዓ/ም) ወጣቱ ደራሲና ገጣሚ ይስማእከ ወርቁ ባጋጠመው የመኪና አደጋ ምክንያት የመናገርና የማስታወስ ክህሎቱን አጥቷል። ይህን የአገር ባለውለተኛ በገቢ በማገዝ በውጭ አገር ሕክምናውን እንዲከታተል ለማድረግ በከተማዋ ወጣት የኪነጥበብ አድናቂዎች አማካኝነት እንቅስቃሴ ተጀምሯል። አዘጋጆቹ የደራሲው ቀዳሚው ስራ በሆነው ”ዴርቶጋዳ” በተሰኘው መጽሐፉ ውስጥ የተጠቀሱትን ...
Read More »በሽንሌ ዞን የሚካሄደውን ተቃውሞ ተከትሎ አካባቢው በመከላከያ ቁጥጥር ስር እንዲውል ተደረገ
በሽንሌ ዞን የሚካሄደውን ተቃውሞ ተከትሎ አካባቢው በመከላከያ ቁጥጥር ስር እንዲውል ተደረገ (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 15 ቀን 2010 ዓ/ም) በሽንሌ ዞን ለተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየውን ተቃውሞ ተከትሎ ወታደራዊ እዙ በቀጥታ የሚያዛቸው ወታደሮች አካባቢውን እንዲቆጣጠሩት መደረጉ ታውቋል። በክልሉ መሪ አቶ አብዲ ኢሌ በቀጥታ የሚታዘዙት የልዩ ሃይል አባላት አካባቢውን ተቆጣጥረው የቆዬ ሲሆን፣ እነዚህን ሚሊሺያዎች በመተካት የክልሉ ኮማንድ ፖስት ከዛሬ ጀምሮ አካባቢውን እንደሚቆጣጠረው ለህዝቡ ...
Read More »የህውሃት ካድሬዎች ትንኮሳ እንዲቆምላቸው የሃይማኖት አባቶች ጠየቁ፡፡
የህውሃት ካድሬዎች ትንኮሳ እንዲቆምላቸው የሃይማኖት አባቶች ጠየቁ፡፡ (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 15 ቀን 2010 ዓ/ም) የህገ መንግስቱን አንቀጾች በትክክል መተርጎም በማይችሉ የህውሃት ካድሬዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የእምነት ቀኖና የሚደረጉ ትንኮሳዎች ይቆምላቸው ዘንድ የእምነት አባቶች ጠየቁ፡፡ በጥንታዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና በመላው ዓለም የሚገኙ የእምነቱ ተከታዮች የሚገለገሉበት የቃልኪዳን ቀለም የያዘ ምልክት የስርዓቱ ካድሬዎች እንደ ባንዲራ በመቁጠር የእምነቱ ተከታዮችን በተለያዩ ጊዜ ...
Read More »የኢንሳው ዳይሬክተር ከስልጣን መነሳታቸውን ተከትሎ መስሪያ ቤቱ ትርምስ ውስጥ ነው
የኢንሳው ዳይሬክተር ከስልጣን መነሳታቸውን ተከትሎ መስሪያ ቤቱ ትርምስ ውስጥ ነው (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 15 ቀን 2010 ዓ/ም) ለኢሳት የደረሰው ጥቆማ እንደሚያመለክተው የዶ/ር አብይ አህመድን ጠ/ሚኒስትር ሆኖ መመረጥ በመቃወም ጄ/ል ተክለብርሃን ወ/አረጋዊ ስልጣናቸውን ከለቀቁ በሁዋላ መስሪያ ቤቱ ትርምስ ውስጥ መግባቱን ምንጮች ገልጸዋል። የመረጃ ደህንነት ኤጀንሲው በአቶ ተመስገን ጥሩነህ እንዲመራ መደረጉ ያበሳጫው የህወሃት ባለስልጣናት፣ የህወሃት የስለላ አባላት ዋና ዋና የሚባሉ የስለላ መሳሪያዎችን ...
Read More »ከአርባ ምንጭ ከተማ በምህረት የተለቀቁት ወጣት ባንተወሰን አበበና ጓደኞቹ እስካሁን ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውን ቤተሰቦቻቸው ተናገሩ
ከአርባ ምንጭ ከተማ በምህረት የተለቀቁት ወጣት ባንተወሰን አበበና ጓደኞቹ እስካሁን ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውን ቤተሰቦቻቸው ተናገሩ (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 15 ቀን 2010 ዓ/ም) ገዥው ህወሃት/ኢህአዴግ የፖለቲካና የሕሊና እስረኞችን በምህረትና በይቅርታ አለመልቀቅ የገባውን ቃል ተከትሎ በነጻ የተለቀቁት የአርባ ምንጭ ወጣቶች ዳግም ለእስራት ተዳርገዋል። ወጣት ባንተወሰን አበበን ጨምሮ አብረውት የነበሩት ሶስት ወጣቶች በባጃጅ ተጭነው ሲጓዙ በፖሊስ ተይዘው ታስረዋል። እስካሁን 14 ቀናት ታስረው ፍርድ ...
Read More »በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጣናን ለመታደግ ማሽን ገዝተው ወደ አገር ቤት ላኩ
በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጣናን ለመታደግ ማሽን ገዝተው ወደ አገር ቤት ላኩ (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 15 ቀን 2010 ዓ/ም) ጣና ሃይቅን ከእንቦጭ አረም ወረራ ለመታደግ በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን 2 ዘመናዊ ማሽኖችን ገዝተው መላካቸውን ለኢሳት ገልጸዋል። ሁለቱ ማሽኖች ካናዳ ከሚገኝ ማሽን አምራች ድርጅት በ92 ሺ 350 የአሜሪካ ዶላር መገዛታቸውን፣ ተጨማሪ ማሽኖችን ለመግዛትም ከባህርዳር ዩኒቨርስቲ ጋር የመስክ ጥናት እያካሄዱ መሆኑን አዘጋጆች ገልጸዋል። ከዚህ ...
Read More »የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማንነት ጉዳይ በህገ መንግስቱ መሰረት ይፈታል ሲሉ ዶ/ር አብይ አህመድ ተናገሩ
የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማንነት ጉዳይ በህገ መንግስቱ መሰረት ይፈታል ሲሉ ዶ/ር አብይ አህመድ ተናገሩ (ኢሳት ዜና ሚያዝያ 12 ቀን 2010 ዓ/ም) አዲሱ ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ ዛሬ ጎንደር ከተማ ተገኝተው ከህዝቡ ጋር ባደረጉት ስብሰባ የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ጥያቄ በህግ ሊፈታ እንደሚችል ህዝቡ ማመን አለበት ብለዋል ፡፡ “ህገ መንግስቱ ይህን ጉዳይ ሊፈታ ይችላል፡፡ በቀጣይም ከወልቃይት ኮሚቴዎች ጋር ውይይት አደርጋለሁ ‘ማለታቸውን የክልሉ ...
Read More »