Amsterdam

የአፋር ክልል ገዥ ፓርቲ አብዴፓ አዲሱን የአቶ አብይ አህመድን አስተዳደር እንዳይቀበል በህወኃት በኩል አፍራሽ ተግባራት እየተፈጸሙ ነው ሲሉ በአውሮፓ የአፋር ማህበረሰብ ተወካይ ገለጹ።

የአፋር ክልል ገዥ ፓርቲ አብዴፓ አዲሱን የአቶ አብይ አህመድን አስተዳደር እንዳይቀበል በህወኃት በኩል አፍራሽ ተግባራት እየተፈጸሙ ነው ሲሉ በአውሮፓ የአፋር ማህበረሰብ ተወካይ ገለጹ። (ኢሳት ዜና ግንቦት 23 ቀን 2010 ዓ/ም) ተወካዩ አቶ ገአስ አህመድ ዛሬ በተለይ ለኢሳት እንደገለጹት ላለፉት 27 ዓመታት በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አቅሙ ክፉኛ የደቀቀው የአፋር ህዝብ እውነተኛ ለውጥ እየጠየቀ ባለበት በአሁኑ ሰዓት ገዥው የአፋር ብሄራዊ ዴሞክራሲ ፓርቲ -ከህወኃት ...

Read More »

የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጋትሎክ ቱት ውጭ አገር ሄደው እንዲታከሙ የክልሉ ካቢኔ ከክልሉ መጠባበቂያ በጀት 1 ሚሊዮን ብር ወጪ እንዲሆን ወሰነ።

የጋምቤላ ክልል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ጋትሎክ ቱት ውጭ አገር ሄደው እንዲታከሙ የክልሉ ካቢኔ ከክልሉ መጠባበቂያ በጀት 1 ሚሊዮን ብር ወጪ እንዲሆን ወሰነ። (ኢሳት ዜና ግንቦት 23 ቀን 2010 ዓ/ም) የክልሉ ምክር ቤት ለክልሉ ፋይናንስ ክፍል በላከው ደብዳቤ ላይ ርዕሰ መስተዳድሩ ዶ/ር ጋትሎክ ቱት ህክምናቸውን በጦር ሃይሎች ሆስፒታል ሲከታተሉ ቢቆዩም፣ ለውጥ ሊታይ ስላልቻለ ወደ ውጭ አገር ሄደው የተሻለ ህክምና እንዲያገኙ 1 ሚሊዮን ...

Read More »

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በ35ኛው የሰሜን አሜሪካ ስፖርት ፌስቲቫል ላይ እንዲገኙ የቀረበው ጥያቄ በማህበሩ በኩል ተቀባይነት ሳያገኝ መቅረቱ ተገለጸ።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በ35ኛው የሰሜን አሜሪካ ስፖርት ፌስቲቫል ላይ እንዲገኙ የቀረበው ጥያቄ በማህበሩ በኩል ተቀባይነት ሳያገኝ መቅረቱ ተገለጸ። (ኢሳት ዜና ግንቦት 23 ቀን 2010 ዓ/ም) ዶክተር አብይ አህመድ በዳላሱ ዝግጅት ላይ እንዲገኙ ጥያቄ የቀረበው በአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በቁጥር ዋሸ 09-620-2010 በጻፈው ደብዳቤ አማካይነት ነው።የማህበሩ አመራሮች ይህን ጥያቄ ተከትሎ ባሰባሰቡት ድምጽ 65 በመቶ ያህሉ ድምጽ ሰጭ እንዲገኙ ፍላጎቱን የገለጸ ቢሆንም፣ ...

Read More »

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ቤተሰቦች ለኢትዮጵያ ህዝብ ምስጋና አቀረቡ

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ቤተሰቦች ለኢትዮጵያ ህዝብ ምስጋና አቀረቡ (ኢሳት ዜና ግንቦት 22 ቀን 2010 ዓ/ም) የግንቦት 7 ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከእስር መፈታታቸውን ተከትሎ ኢትዮጵያን ላዳረጉት ድጋፍ ቤተሰቦቻቸው ምስጋናቸውን ገልጸዋል። የአቶ አንዳርጋቸው ባለቤት ወ/ሮ የምስራች ሃይለማርያም እንዲሁም ታላቅ እህቱ ወ/ሮ ብዙአየሁ ጽጌ፣ ደስታቸውን በመግለጽ፣ ላለፉት 4 አመታት ህዝቡ ሲያደርገው ለነበረው ትግል ደስታቸውን ገልጸዋል። በሌላ በኩል ደግሞ አርበኞች ግንቦት7 በአቶ ...

Read More »

ከቤንሻንጉል ጉሙዝና ኦሮምያ ክልል የተፈናቀሉ የአማራ ተወላጆች የመፍትሄ ያለህ እያሉ ነው

ከቤንሻንጉል ጉሙዝና ኦሮምያ ክልል የተፈናቀሉ የአማራ ተወላጆች የመፍትሄ ያለህ እያሉ ነው (ኢሳት ዜና ግንቦት 22 ቀን 2010 ዓ/ም) በመቶዎች የሚቆጠሩ ከቤንሻንጉል ጉሙዝና ከኦሮምያ ክልል ቡኖ በደሌ ወረዳ የተፈናቀሉ የአማራ ተወላጆች በአሁኑ ሰዓት በባህርዳር ከተማ በጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን እንዲሁም በተለምዶ አባይ ማዶ እየተባለ በሚጠራው በምግብ ዋስትና ግቢ ውስጥ ተጠልለው ይገኛሉ። በምግብ ዋስትና ግቢ ውስጥ ተጠልለው የሚገኙት ተፈናቃዮች፣ ከሳምንታት በፊት ወደ ትውልድ ቀያቸው ...

Read More »

በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ ነው

በኢህአዴግ አባል ድርጅቶች መካከል ያለው ልዩነት እየሰፋ ነው (ኢሳት ዜና ግንቦት 22 ቀን 2010 ዓ/ም) በኢትዮጵያ የሚካሄደውን የለውጥ እንቅስቃሴ ለማፈን ነባር የብአዴን እና የህወሃት አባላት በሙሉ ሃይላቸው እየተንቀሳቀሱ ነው። ለውጥ የሚፈልጉ የኢህአዴግ አባላት ቁጥራቸው እየጨመረ ቢሆንም፣ ነባር የኢህአዴግ አመራሮች ከአዲሶቹ የድርጅቱ አመራሮች ጋር ተስማምተው ለመጓዝ ተቸግረዋል። ህወሃት በብአዴን ውስጥ ያለውን ክፍፍል ለራሱ ጥቅም ለማዋል እየተንቀሳቀ ሲሆን በተለይ የለውጡን እንቅስቃሴ አይደግፉም ...

Read More »

“ፍርዱን ተፈጻሚ አድርጉትና ሰው እየሳቀ እንደሚሞት ላሳያችሁ እያልኩ ደህንነቱን ጠይቄያቸዋለሁ” ሲሉ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ተናገሩ

“ፍርዱን ተፈጻሚ አድርጉትና ሰው እየሳቀ እንደሚሞት ላሳያችሁ እያልኩ ደህንነቱን ጠይቄያቸዋለሁ” ሲሉ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ተናገሩ (ኢሳት ዜና ግንቦት 21 ቀን 2010 ዓ/ም) ዛሬ ከእስር ተለቀው ከቤተሰቦቻቸው እና ከደጋፊዎቻቸው ጋር የተገናኙት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ፣ ደህንነቶች ምርምራ ቢያመደርጉበት ወቅት፣ በእንዲህ አይነት አገር ከምኖር ፍርድ ቤት የወሰነውን የሞት ፍርድ ቤት ፈርዳችሁ እንድትገድሉኝ፣ ዛሬም እዚህ ቁጭ ብዬ የምናገረው ፍርድ ቤት የወሰነውን ውሳኔ በአስቸኳይ ...

Read More »

ከአራት ዓመታት በፊት የዓለምአቀፍ ሕግን በሚጻረር መልኩ ከየመን ዓለምአቀፍ አየር ማረፊያ ታግተው የተወሰዱት የነፃነት ታጋዩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከእስር እንደተፈቱ በስፋት ቢነገርም ከመንግስት፣ከቤተሰቦቻቸውም ሆነ ከእንግሊዝ ኤምባሲ ዘንድ ማረጋገጥ አልተቻለም።

ከአራት ዓመታት በፊት የዓለምአቀፍ ሕግን በሚጻረር መልኩ ከየመን ዓለምአቀፍ አየር ማረፊያ ታግተው የተወሰዱት የነፃነት ታጋዩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከእስር እንደተፈቱ በስፋት ቢነገርም ከመንግስት፣ከቤተሰቦቻቸውም ሆነ ከእንግሊዝ ኤምባሲ ዘንድ ማረጋገጥ አልተቻለም። (ኢሳት ዜና ግንቦት 20 ቀን 2010 ዓ/ም) አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በህገወጥ መንገድ ከታገቱበት ጊዜ አንስቶ በሀገር ውስጥም ሆነ በመላው ዓለም የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በተቃውሞ ሰልፎችና በተለያዩ መድረኮች ተቃውሟቸውን ሲገልጹ ቆይተዋል። ከዚህም ባሻገር ...

Read More »

የዘንድሮው ግንቦት 20 ካለፉት 27 ዓመታት በተለየ መልኩ ያለ ፉከራና ቀረርቶ ታስቦ ውሏል።

የዘንድሮው ግንቦት 20 ካለፉት 27 ዓመታት በተለየ መልኩ ያለ ፉከራና ቀረርቶ ታስቦ ውሏል። (ኢሳት ዜና ግንቦት 20 ቀን 2010 ዓ/ም) አገዛዙ በየዓመቱ ግንቦት 20 በመጣ ቁጥር ህዝብን በተደጋጋሚ አሰልቺ ፕሮፓጋንዳ ሲያደነቁር የቆዬ ሲሆን ፣ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ስላለፈው ስርዓትም ሆነ ስለ ነጻነት ዕለትነቱ ፕሮፓጋንዳ ሳይነዛ እንዲያልፍ ተደርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድም በሰጡት መግለጫ “ዕለቱን የእረፍት እናድርገው” ከማለት ውጭ እስከዛሬ በሹመኞች ሲባል ...

Read More »

በኮሬና ጉጂ ብሄረሰቦች መካከል እየተካሄደ ባለው ግጭት የሰዎች ህይወት እየጠፋ ነው።

በኮሬና ጉጂ ብሄረሰቦች መካከል እየተካሄደ ባለው ግጭት የሰዎች ህይወት እየጠፋ ነው። (ኢሳት ዜና ግንቦት 20 ቀን 2010 ዓ/ም) መቋጫ ያልተገኘለት በአማሮ ወረዳ በሚኖሩ የኮሬና አዋሳኝ አካባቢዎች የሚኖሩ ጉጂዎች መካከል ከድንበር ማካለል ጋር በተያያዘ ከ11 ወራት በላይ የወሰደው ደም አፈሳጭ ግጭት ሰሞኑን አገርሽ 6 የኮሬ ብሄረሰብ አባላት ሲገደሉ ከ10 በላይ ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል። እስካሁን ባለው ግጭት በከሮ በኩል ከ50 ያላነሱ ሰዎች ...

Read More »