በምስራቅ ኦሮምያ አካባቢ በሶማሊ ልዩ ሃይል አባላትና በኦሮምያ ፖሊስ መካከል የተኩስ ልውውጥ ተካሄደ ( ኢሳት ዜና ነሐሴ 22 ቀን 2010 ዓ/ም ) በምስራቅ ኦሮምያ ባቢሌ ወረዳ የሶማሊ ልዩ ሃይል አባላት ወደ ገጠር በመግባት በህዝቡ ላይ ጥቃት በመክፈት ጉዳት ማድረሳቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። የኦሮምያ ፖሊስ በወሰደው የመከላከል እርምጃ 7 ወታደሮች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። የልዩ ሃይል አባላቱ 2 የኦሮምያ ፖሊሶችን መምታታቸው ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
በመርጦ ለማርያም 44 የካቢኔ አባላት በህዝቡ ታገዱ
በመርጦ ለማርያም 44 የካቢኔ አባላት በህዝቡ ታገዱ ( ኢሳት ዜና ነሐሴ 22 ቀን 2010 ዓ/ም ) የከተማዋ ነዋሪዎች ተቃውሞ ማካሄዳቸውን ተከትሎ ከክልል ተወክለው የመጡ ባላስልጣናት ያነጋገሩዋቸው ቢሆንም፣ ነዋሪዎቹ ሁሉም የካቢኔው አባላት ከስልጣን እንዲወርዱላቸው ጠይቀዋል። ጥያቄውን ተከትሎ አስተዳዳሪው የማትፈልጉን ከሆነ ሁላችንም ስልጣናችንን እንለቃለን ያሉ ሲሆን፣ የተወሰኑ የአካቢኔ አባላትን ለማቆየት የተደረገው ሙከራ ተቃውሞ እንዳጋጠመውና ህዝቡ ሁሉም አመራሮች ካልወረዱና በሌሎች ሰዎች ካልተተኩ እንደማይቀበል ...
Read More »በቤንች ማጂ ዞን በማጂ ወረዳ ተገንብቶ የተጠናቀቀ ሆስፒታል ስራ ባለመጀመሩ ህዝቡ ምሬቱን እየገለጸ ነው
በቤንች ማጂ ዞን በማጂ ወረዳ ተገንብቶ የተጠናቀቀ ሆስፒታል ስራ ባለመጀመሩ ህዝቡ ምሬቱን እየገለጸ ነው ( ኢሳት ዜና ነሐሴ 22 ቀን 2010 ዓ/ም ) የአካባቢው ነዋሪዎች እንደሚሉት የዞኑ ዲዛይን እና ኮንስትራክሽን መምሪያ እና ግንባታውን ያከናወነው ድርጅት ርክክብ ባለመፈፀማቸው ሆስፒታሉ አገልግሎት መስጠት አልቻለም። የጤና ባለሙያዎች የተመደቡ ቢሆንም፣ አገልግሎት መስጠት አልቻሉም። ለተከታታይ ህክምና ታማሚዎች ህክምና እየተሰጠ ያለው ከ 40 አመት በላይ እድሜ ባለው ...
Read More »መንግስት ቪ8 እየተባሉ የሚጠሩ መኪኖችን ከተማ ውስጥ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ አገደ
መንግስት ቪ8 እየተባሉ የሚጠሩ መኪኖችን ከተማ ውስጥ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ አገደ ( ኢሳት ዜና ነሐሴ 22 ቀን 2010 ዓ/ም ) የመንግስት ባለስልጣናት ከ5 እስከ 6 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ዋጋ ያላቸውን እጅግ ውድ መኪኖች የሚያሽከረክሩ ሲሆን፣ መኪኖቹ ለመስክ ስራ ካልሆነ ከተማ ውስጥ ጥቅም ላይ እንዳይውሉ እገዳ መጣሉን የመንግስት ግዢና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት አቶ ይገዙ ዳባ ለመንግስት የመገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል። ለመንግስት ባለስልጣናት ...
Read More »ሴናተር ጆን ማኬይ በቀብር ስነስርአታቸው ላይ ትራምፕ እንዳይገኙ ተናዘዙ
(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 21/2010) ባለፈው ቅዳሜ ከዚህ አለም በሞት የተለዩት የአሪዞናው ሴናተር ጆን ማኬይ በቀብር ስነስርአታቸው ላይ የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዳይገኙ መናዘዛቸው ተሰማ። ጆን ማኬይ በቀብር ስነስርአታቸው ላይ እንዲገኙ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማና ጆርጅ ደብሊው ቡሽ እንዲገኙላቸው በክብር ጋብዘዋል። ነገር ግን ፕሬዝዳንት ትራምፕ በቀብር ስነስርአቴ ላይ እንዲገኙ አልፈግም ሲሉ ማኬይ እቺን ምድር ከመሰናበታቸው በፊት መናዘዛቸውን ሲ ኤን ኤን በዘገባው አስፍሯል። ...
Read More »የዛላ አንበሳ ድንበር በዜጎች ስምምነት ተከፈተ
(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 21/2010) ለበርካታ አመታት ሲያወዛግብ የቆየው የዛላ አንበሳ ድንበር በዜጎች ስምምነት መከፈቱ ተሰማ። ይህንን ተከትሎም የሃይማኖት አባቶችን፣የሃገር ሽማግሌዎችን፣ሴቶችንና ወጣቶችን ያካተተ ቡድን በኤርትራዋ የንግድ ከተማ ሰናፌ ወደ ምትገኘው ሰርሃ ከተማ መጓዙ ተሰምቷል። 40 አባላትን አካቷል የተባለው ቡድን ከዛላአንበሳ አለፍ ብላ ወደ ምትገኘው ሰርሃ ከተማ ሲገባም በኤርትራ ወታደሮች አቀባበል ተደርጎለታልነው የተባለው ከሁለት አስርት አመታት በላይ የዘለቀው የጸብ ግድግዳ ፈርሶ ሰላምና አንድነት ...
Read More »የአርበኞች ግንቦት ሰባት ጳጉሜ አራት አዲስ አበባ ይገባል ተባለ
(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 21/2010) የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራሮችንና አባላትን ለመቀበል በአዲስ አበባ የተዋቀረው ኮሚቴ ዝግጅቱን አጠናክሮ መቀጠሉን አስታወቀ። በመላው ዓለም ያሉት የንቅናቄው አመራርና አባላት ጳጉሜን አራት አዲስ አበባ እንደሚገቡ ለማወቅ ተችሏል። ትላንት በአዲስ አበባ የስብሰባ ማዕከል በተካሄደው የአቀባበል ኮሚቴው ህዝባዊ ስብሰባ ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች መገኘታቸው ታውቋል። ድምጻዊ አለማየሁ እሸቴን ጨምሮ ጋዜጠኞችና አክቲቪስቶች የንቅናቄውን አመራሮች ፎቶግራፍ የሚገኝበት ቲሸርት በመልበስ ...
Read More »አቶ በረከት ስምዖን የመንቀሳቀስ መብቴ ተገድቧል አሉ
(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 21/2010) የቀድሞ የብአዴን ከፍተኛ አመራርና የኢህአዴግ ቁልፍ ሰው አቶ በረከት ስምዖን የመንቀሳቀስ መብቴ ተገድቧል ሲሉ ገለጹ። ታዲያስ አዲስ ከተሰኘ የሬዲዮ ፕሮግራም ጋር ባደረጉት ቃለመጠይቅ አሁን ባለው ሁኔታ በሀገሪቱ የተለያዩ ቦታዎች ለመንቀሳቀስ ገደብ ተጥሎብኛል ብለዋል። አቶ በረከት የመንቀሳቀስ መብታቸውን የገደበው የመንግስት አካል ይሁን ሌላ በግልጽ ያስቀመጡት ነገር የለም። የብአዴን የአሁኑን አመራር ክፉኛ የወቀሱት አቶ በረከት ስምዖን የተበላሹ አመራሮች ናቸው ...
Read More »ብአዴን ወሳኝ የሚባሉ ርምጃዎችን መውሰድ ጀመረ
(ኢሳት ዜና–ነሐሴ 21/2010) የብሔረ አማራ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ብአዴን/ በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን የለውጥ ጉዞ አጠናክሮ ለማስቀጠል ወሳኝ የሚባሉ ርምጃዎችን መውሰድ ጀመረ። በዚሁም መሰረት የድርጅቱ መተዳደሪያ ደንብ እንደሚሻሻልና የድርጅቱ ስያሜም እንደሚለወጥ ገልጿል። የድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ ባወጣው ያልተለመደ መግለጫ ብአዴን የሚመራበትን ርዕዮት ሊቀይር እንደሚችል አስታውቋል። ድርጅቱ የግለሰብ መብትና የቡድን መብት ተጣጥመው እንዲከበሩ ጠይቋል። የክልል አስተዳደራዊ ወሰኖች እንደገና እንዲሻሻሉ እንደሚታገልም ነው ባወጣው መግለጫ ያስታወቀው። በዚሁም ...
Read More »አቶ አብዲ ኢሌ በተለያዩ ወንጀሎች ይጠየቃሉ ተባለ
(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 21/2010) የሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ አብዲ መሀመድ ዑመር አብዲ ዒሌ የሰብዓዊ መብት ጥሰትን ጨምሮ በተለያዩ ወንጀሎች እንደሚጠየቁ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታወቀ። አቶ አብዲ ዒሌ ዛሬ አዲስ አበባ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ እንዳሉ በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም ፖሊስ አስታውቋል። እሳቸውና ሌሎች ሰባት የሶማሌ ክልል የቀድሞ አመራሮችና ግለሰቦችም ያለመከሰስ መብታቸው መነሳቱም ተገልጿል። አቶ አብዲ ዒሌ በተያዙበት ወቅት በመኖሪያ ቤታቸው ...
Read More »