.የኢሳት አማርኛ ዜና

የወልድያ ነዋሪዎች አገራችሁንና ባንዲራችሁን አድኑ የሚል ጥሪ ቀረበላቸው

ነሃሴ ፩(አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በድምጻችን ይሰማ የሙስሊም ኢትዮጵያውያን እንቅስቃሴ ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ የገባው መንግስት ፣ በካድሬዎቹ አማካኝነት ” የአገርህ ባንዲራ ተደፍራለችና ስልፍ ውጣ እያለ” ትናንት ህዝቡን ሲያስፈርም መዋሉን የአይን እማኞች ገልጸዋል። አንዳንድ ካድሬዎች “ጊዮርጊስ አድዋ ድረስ ሄዶ ተዋግቷል፣  አንተም አገር ሊያጠፉ የመጡትን ተነስትህ ተዋጋ”የሚሉ ቅስቀሳዎችን መዋላቸውንም እነዚሁ እማኞች ተናግረዋል። በእድሜ ለገፉት ደግሞ አሸባሪዎችን ለመቃወም ከወጣችሁ እርዳታ እንሰጣችሁዋላን በማለት ...

Read More »

በአዲስአበባ የኢታኖል ድብልቅ ቤንዚን ዋጋ ጨመረ

ነሃሴ ፩(አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዓለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ ባልጨመረበት ሁኔታ በአዲስ አበባ ብቻ የኢታኖል ቤንዚን ድብልቅ ነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በ0.16 ሳንቲም ከፍ በማለት በሊትር 18 ብር ከ94 ሳንቲም እንዲሸጥ የንግድ ሚኒስቴር መወሰኑን አስታወቀ፡፡ ሚኒስቴሩ እንዳመለከተው የዓለም የነዳጅ ዋጋ የመዋዥቅ ሁኔታ ማሳየቱን ተከትሎ ጭማሪ ለማድረግ መገደዱን ይግለጽ እንጂ በዓለም ገበያ በዚህ ወቅት ነዳጅ ዋጋ የተለየ ጭማሪ አለማሳየቱን የዜና ...

Read More »

ከ192 ሚሊዮን ብር በላይ የወጣበት ከሾላ ገበያ ለም ሆቴልን የሚሻገረው አዲስ መንገድ በከፊል ሊፈርስ ነው ተባለ

ነሃሴ ፩(አንድ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለቀላል ባቡር ፕሮጀክቱ ግንባታ በሚል ሰበብ ከዚህ ቀደም እንዲፈርሱ ከተደረጉት ከመስቀል አደባባይ ቃሊቲ የሚዘልቀው መንገድ የመሀል ክፍልና ከደሴ ሆቴል ወደ ፑሽኪን አደባባይ ከተዘረጋው አዲስ ከፊል የአስፓልት መንገድ በተጨማሪ ፣ ከ192 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጐበት ከሾላ ገበያ በለም ሆቴል እስከ አንበሳ ጋራዥ የተገነባው መንገድ የተወሰነ ክፍሉ በቅርቡ እንደሚፈርስ ሪፖርተር ዘግቧል። ከ20 ዓመታት በላይ አገልግሎት ...

Read More »

ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ የፀረ ሽብር ህጉን የመቃወም እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከእስር ቤት ሆና ባስተላለፈችው መልዕክት ጠየቀች

ነሀሴ ፩ ቀን ፩፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ከሰኔ 2003 ዓ.ም. ጀምሮ በእስር ላይ የምትገኘው ጋዜጠኛ ርዮት አለሙ እየተካሄደ ያለው የፀረ ሽብር ህጉን የመቃወም እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከእስር ቤት ሆና ባስተላለፈችው መልዕክት ጠየቀች፡፡ ከቃሊቲ ማረሚያ ቤት በጻፈችው ደብዳቤ ጋዜጠኛ ርዩት አለሙ ገዥው የኢህአዴግ መንግስት የፀረ ሽብር ህጉን ለስልጣኑ ማራዘሚያነት ኢፍትሃዊ በሆነ መንገድ እየተጠቀመበት እንደሚገኝ ገልጻ እየተደረጉ ያሉት የተቃውሞ ሰልፎችና ሌሎችም ሰላማዊ የተቃውሞ ...

Read More »

ከፍተኛው ፍርድ ቤት ባለ አምስት ኮከብ የሆነውን ኢንተርኮንቴነንታል ሆቴል እና ሌሎች ህንጻዎችን ከሙስና ከተጠረጠሩ ባለሀብቶች ተወስደው በገለልተኛ ወገን እንዲተዳደሩ ውሳኔ አስተላለፈ፡፡

ነሀሴ ፩ ቀን ፩፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ፍርድ ቤቱ በትላንትናው እለት የፌደራሉ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን አቃቢ ህግና የተጠርጣሪ ጠበቆች በጋራ ተስማምተው ንብረቱን የሚያስተዳድር አካል እስከ መስከረም 22 ቀን 2006 ዓ.ም. እንዲያቋቁሙ ትዕዛዝ አስተላልፏል፡፡ ንብረታቸው በገለልተኛ አካል እንዲተዳደር ፍርድ ቤት የወሰነባቸው ንብረትነቱ የአቶ ሰማቸው ከበደ የሆነው ባለ 5 ኮከብ ኢንተርኮንተነንታል ሆቴል እና ዲ ኤች ሲሜክስ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እንዲሁም ...

Read More »

መንግስት ሰሞኑን የሚከበረውን የኢድ አልፈጥር በዓል በመግቢያ ካርድ እንዲሆን ያስተላለፈውን መመሪያ በልዩ ትዕዛዝ እንዲቆም ማድረጉን ለኢሳት ከአዲስ አበባ የደረሱ መረጃዎች አመለከቱ

ነሀሴ ፩ ቀን ፩፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-መንግስት በትላንትናው ዕለት የህዝበ ሙስሊሙን የተቃውሞ ስልፍ በመፍራት በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚከበረውን በአል በልዩ የመግቢያ ካርድ እንዲሆን በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የመግቢያ ካርዶችን እንዳዘጋጀ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ይሁንና ዛሬ የፌደራል መረጃና ደህንነት መስሪያ ቤት ልዩ ትዕዛዝ በመስጠት ሁኔታው እንዲቆም ማድረጉ ታውቋል፡፡ የፌደራል መረጃና ደህንነት ተወካዮች በአዲስ አበባ አስሩም ክፍለ ከተማ የሚገኙ የመጅሊስ አባላትን፣ ካድሬዎችና የደህንነት ሰዎችን ...

Read More »

ጉግል የአበበ ቢቂላን ፎቶ በፊት ገጹ ላይ በማስቀመጥ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ተጠቃሚዎች አስበውት እንዲውሉ አደረገ

ነሀሴ ፩ ቀን ፩፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የታዋቂው የአበበ ቢቂላ 81ኛ ዓመት የልደት በዓል በማስመልከት ታዋቂው የድህረ ገጽ ቋት የሆነው ጉግል የአበበ ቢቂላን ፎቶ በፊት ገጹ ላይ በማስቀመጥ በመቶ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ተጠቃሚዎች አስበውት እንዲውሉ አደረገ፡፡ የጉግል አካል የሆነውና ጉግል በአርማነት የሚጠቀመው ጉግል ዶድል ድረ ገጽ ላይ የመጀመሪያው የሰብ ሰሀራ ኦሎምፒክ አሸናፊ የሆነው አበበ ቢቂላ እንደዚህ አይነት ክብርን ሲያገኝ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ አትሌት ...

Read More »

120 ኢትዮጵያዊያንና ኤርትራውያንን የያዘች መርከብ በማልታና ጣሊያን መንግሥታት ወደ ግዛቴ አላስገባም በሚል ውዝግብ በእንግልት ላይ ናቸው

ነሀሴ ፩ ቀን ፩፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ሁኔታው ያሳሰበው የአውሮፓ ህብረት የማልታ መንግስት ያለምንም መዘግየት በእንግልት ላይ የሚገኙትን ሰዎች ወደ ድንበሩ ገብተው ሰብአዊ መብት እንዲያገኙ ጠይቋል፡፡ ማረፊያ ያጣችው መርከብ በውስጧ አራት እርጉዝ ሴቶችን፣ አንድ የተጎዳች ሴትና የ5 ወር ህጻን መያዟን የአውሮፓ ህብረት አስታወቋል፡፡ በላይቤሪያ መንግስት ንብረትነት የተመዘገበችው ጀልባ በግሪካዊ ኩባንያ አገልግሎት በመስጠት ላይ የነበረች ሲሆን 120 ኢትዮጵያውያኑንና ኤርትራዊያኑን በሊቢያ ቀይ ባህር ...

Read More »

በቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ የተገጣጠሙ የህዝብ አውቶብሶች አመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ60 በመቶ በላይ የሚሆኑት ተበላሹ

በቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ የተገጣጠሙ የህዝብ አውቶብሶች አመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ60 በመቶ በላይ የሚሆኑት ተበላሹ ሐምሌ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የቢሾፍቱ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት ያመረታቸው እና የገጣጠማቸው የከተማ እና  አገር አቋራጭ  አውቶብሶች አመት ሳይሞላቸው ለጉዳት ተደርገዋል። አውቶብሶቹ ከግማሽ በላይ አካላቸው በሀገር ውስጥ ሙሉ ለሙሉ የተመረተ ቢሆንም በውጭ ሃገር ግዥ የተፈፀመው የሞተር አካላቸው ግን ምንም ...

Read More »

መንግስት በምእራብ አርሲ ዞን የተገደሉትን ሙስሊሞች ቁጥር መቀነሱን የአካባቢው ሰዎች ገለጹ

ሐምሌ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በምእራብ አርሲ ዞን በኮፈሌና አካባቢዋ የፌደራል ፖሊሶች በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ላይ በወሰዱት እርምጃ 3 ሰዎች መገደላቸውና 7 ሰዎች መቁሰላቸውን የኦሮምያን ፖሊስ በመጥቀስ የመንግስት የመገናኛ ብዙሀን ቢዘግቡም የኢሳት ምንጮች በበኩላቸው የሟቾች ቁጥር ከ18 እስከ 25 ይደርሳል ይላሉ። በአካባቢው የሚገኝ አንድ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የሟቾችን ቁጥር 18 መሆኑን ሲገልጽ፣ ወደ ኮፈሌ እና ዋቢ ከተሞች ለመግባት ሙከራ ...

Read More »