ጥቅምት ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአለማቀፍ የወንጅል ፍርድ ቤት 50 አመታት የተፈረደባቸው ቻልረስ ቴለር በዛሬው እለት ለእንግሊዝ ፍርድ ቤት ተላልፈው የተሰጡ ሲሆን፣ በሩዋንዳ እንዲታሰሩ ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ተድርጎባቸዋል። ፕሬዞዳንቱ በሴራሊዮን ለተፈጸመው የጦር ወንጀል እጃቸው አለበት በሚል ዘሄግ የሚገኘው የወንጀል ፍርድ ቤት አምና የ50 አመታት እስር እንደፈረደባቸው ይታወቃል።
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በነገው ኢድ-አል አድሃ ላይ ተቃውሞ እንደሚያሰሙ ታወቀ
ጥቅምት ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ለወራት ተቋርጦ የነበረው የድምጻችን ይሰማ ተቃውሞ ነገ በመንግስት ባለስልጣናትና በመጅሊስ መሪዎች ንግግር ላይ ተግባራዊ እንደሚሆን ከወጣው መርሀግብር ለማወቅ ተችሎአል። በአዲስ አበባ ስታዲየም በሚካሄደው ዝግጅት የመንግስት ባለስልጣናትም ሆኑ የመጅሊስ አመራሮች ንግግር የሚያደርጉ ከሆነ ንግግሩ እስኪቆም ድረስ ተቃውሞው ይቀጥላል። ተቃውሞው በመላ አገሪቱ እንደሚከናወን ድምጻችን ይሰማ ያወጣው መረጃ ያመለክታል። ፖሊስ ጸጥታ ለማስከበር ዝግጅት ማድረጉን የፌደራል ፖሊስ ባወጣው ...
Read More »የደብረማርቆስ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ተቃውሞ አሰሙ
ጥቅምት ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አዲሱን የትምህርት አመት ለመጀመር ምዝገባ ያጠናቀቁት ተማሪዎች ፣ ከአለባበስ ጋር በተያያዘ ባነሱት ተቃውሞ የግቢው መስታውቶችና አንዳንድ አገልግሎት መስጪያ እቃዎች መሰባበራቸው ታውቋል፡፤ ይህንንም ተከትሎ ፖሊስ ግቢውን መቆጣጠሩን ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ተማሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። የተቃውሞው መነሻ የዩነቨርስቲው ባለስልጣናት ከቤተከርስቲያን መልስ ነጠላ ለብሰው ወደ መመገቢያ ክፍል የገቡትን ተማሪዎች ፣ ነጠላ ለብሳችሁ መግባት አትችሉም በማለት በመከልከላቸው ነው ። ...
Read More »አቶ አዲሱ ለገሰ አራት ምክትሎች ተመደቡላቸው
ጥቅምት ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሕአዴግ ካድሬዎችን ለማሰልጠን የተገነባውን የፖለቲካ ማሠልጠኛ ተቋም በሚኒስትር ማዕረግ ሲመሩ የነበሩት አቶ አዲሱ ለገሰ ከኢህአዴግ አባል ድርጅቶች የተውጣጡ ምክትሎች ተሹመውላቸዋል፡ ፡ ከብአዴን አቶ ለገሰ ቱሉ፣ ከደሕዴን አቶ ወንድሙ ገዛኸኝ፣ ከሕወሓት አቶ ነጋ በርሄ ሲሆኑ፣ ከኦሕዴድ የተወከለው አመራር እስካሁን አለመታወቁን ሪፖርተር ዘግቧል። ማሠልጠኛ ማዕከሉ በስድስት ዙሮች በርካታ ካድሬዎችን ያሰለጠነ መሆኑን የዘገበው ጋዜጣው፣ ካድሬዎቹም ከሥልጠና በኋላ ...
Read More »ከሶስት ሚልየን በላይ ዜጎች ለወባ ወረርሽኝ ተጋልጠዋል
ጥቅምት ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የክረምቱን መውጣት ተከትሎ ወባ በሚያጠቃቸው ወረዳዎች ወረርሺኙ መከሰቱን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። በገዳይነቱ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ደረጃ የሚይዘው የወባ በሺታ በአሁኑ ስዓት በአርሶ አደሩ ህይዎት ውስጥ ፈታኝ መሆኑን ከሁሉም ክልሎች ለፌድራል ጤና ጥበቃ ሚኒስትር የተላለፈው መረጃ ያመለክታል፡፡ በበሺታው ፈውስ አጥተናል የሚሉት ኗሪዎች ከገበያ እንደ ሸቀጥ እቃ የሚገዙዋቸው መዳህኒቶች የማዳን አቅም የላቸውም ይላሉ፡፡ በኢትዩጵያ የረጅ ድርጁቶች ...
Read More »የሞይ ኢብራሂም ፋውንዴሽን ለ5ኛ ጊዜ ለሽልማት የሚበቃ የአፍሪካ መሪ ማጣቱን አስታወቀ
ጥቅምት ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሱዳናዊው ቱጃር ሞ ኢብራሂም የተቋቋመው የሞ ፋውንዴሽን መልካም አስተዳደርን ያሰፈረ፣ ስልጣኑን በሰላም ለለቀቀ የአፍሪካ መሪ 5 ሚሊዮን ዶላር በሽልማት መልክ ይሰጣል። በዚህ አመትም ለ4ኛ ጊዜ አሸናፊ የሚሆን የአፍሪካ መሪ አልተገኘም። እስካሁን ድረስ ሽልማቱን ያሸነፉት የኬፕ ቨርዴው ፔድሮ ቬሮና ፓይሬስ፣ የቦትስዋናው ፌስተስ ሞጋኤና የሞዛምቢኩ ጆአኪም ቺሳኖ ናቸው።
Read More »አንድ የናይጀሪያ ተጫዋች በኢትዮጵያ ደጋፊዎች መመታቱ ተዘገበ
ጥቅምት ፬(አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቢቢሲ ባወጣው ዘገባ እንደገለጸው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በናይጀሪያ ቡድን መሸነፉ ያበሳጫቸው ደጋፊዎች የናይጀሪያን ቡድን አሳፍሮ ሲጓዝ በነበረው አውቶቡስ ላይ ድንጋይ በመወርወር አንድ ተጫዋች አቁስለዋል። ኖሳ ኢግቦር የተባለው ተጫዋች መዳፉ አካባቢ መመታቱን የዘገበው ቢቢሲ፣ የናይጀሪያ ቡድን ባለስልጣናት ክስተቱን ለአለማቀፉ እግር ኳስ ፌደሬሽን ማሳወቃቸውንም ገልጿል። ድርጊቱን ተከትሎ ምናልባትም ፊፋ በኢትዮጵያ ላይ ቅጣት ሊጥል ይችላል። በሌላ ዜና ...
Read More »ከ15 ሺ በላይ የኢህአዴግ አባላት መልቀቂያ አስገቡ
ጥቅምት ፩(አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢህአዴግ እያካሄደ ባለው የአባላት ግምገማ ወቅት ከ15 ሺ በላይ አባላት በአንድ ጊዜ መልቀቂያ ማስገባታቸው ይፋ ተደርጓል። ስራቸውን ከሚለቁበት ምክንያቶች መካከል በድርጅቱ አመኔታ ማጣት ፣ ተገቢውን አገልግሎት ክፍያ አለማግኘት፣ ለድርጅቱ የሚከፍሉት ገንዘብ ከፍተኛ መሆን እና የድርጅቱ አባላት ሹመት በወገን መሆኑ የሚሉት ተጠቅሰዋል። ከፍተኛ የአባላት መልቀቂአ ቁጥር ከተመዘገበባቸው ክልሎች መካከል ኦሮሚያ በ9 ሺ 4 መቶ 56 ...
Read More »እ.ኤ.አ በ2020 የአፍሪካ ምርጥ በተመንግስት መሆን ራዕይ ሰነቀው የቤተመንግስት አስተዳደር ለተሰናባቹ ፕሬዚደንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ ለሁለተኛ ጊዜ የተከራየው በወር 400 ሺ ብር ፣ በዓመት 4 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር የሚያወጣ መኖሪያ ቤት ኮንትራቱ እንዲሰረዝ ተወሰነ፡፡
ጥቅምት ፩(አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አስተዳደሩ ቀደም ሲል በወር 530 ሺ ብር ገደማ ቤት በመከራየት ውል ከፈጸመ በኋላ ከሕዝብ በተከታታይ ተቃውሞ መሰማቱን ተከትሎ እንዲሰረዝ በመወሰን ለሁለተኛ ጊዜ 400 ሺ ብር የሚያወጣ ቤት በአዲስአበባ አክሱም ሆቴል አካባቢ መከራየቱ ሌላ ተቃውሞና ውግዘትን እያስከተለበት ይገኛል፡፡ አስተዳደሩ ፕሬዚደንቱ በመስከረም ወር 2006 ስልጣን እንደሚያስረክቡ አስቀድሞ እያወቀ ምንም ዓይነት ዝግጅት ሳያደርግ በመጨረሻው ሰዓት ወደቤት መከራየት ...
Read More »አፍሪካ ህብረት የዓለማቀፉን የወንጀኞች ፍርድ ቤት ወቀሰ
ጥቅምት ፩(አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዓለማቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ፍትሀዊ ባልሆነ መልኩ በ አፍሪካ ላይ ስጋት እያሳደረ ነው ሲሉ አንድ ከፍተኛ የህብረቱ ባለስልየጣን መናገራቸውን ቢቢሲ ዘገበ። የኢትዮጵያው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ቴዎድሮስ አድሀኖም ይህን ያሉት፤ዛሬ በአዲስ አበባ በተጀመረው የህብረቱ ልዩ ስብሰባ ላይ ነው። ቴዎድሮስ በስብሰባው ላይ ፦”ፍርድ ቤቱ ያነጣጠረው አፍሪካ ላይ ነው።”ማለታቸውን የገለጸው ቢቢሲ፤ በስብሰባው አፍሪካ ከዓለማቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ...
Read More »