.የኢሳት አማርኛ ዜና

የኢትዮጵያው አገዛዝ የውጭ ብድር ቁጥጥር ያድርግ ተባለ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 5/2010) የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ዋና ዳይሬክተር ክርስቲን ላጋርድ የኢትዮጵያ መንግስት የውጭ ብድር ቁጥጥር እንዲያደርግና የወጭ ምርቶች ተወዳዳሪነትን እንዲያሰፋ ጠየቁ። ኢትዮጵያ ይህን ርምጃ ካልወሰደች ከፍተኛ የኢኮኖሚ ቀውስ ሊገጥማት እንደሚችል ዳይሬክተሯ አሳስበዋል። የአገዛዙ ቃለ አቃባዮች ግን የዳይሬክተሯ ጉብኝት ኢትዮጵያ አለም አቀፍ ተሰሚነቷ በመጨመሩና ኢኮኖሚዋ በማደጉ የተካሄደ ነው ሲሉ የተሳሳተ መግለጫ ሰጥተዋል። በኢትዮጵያ የገንዘብና የእህል ዋጋ ግሽበት በእጅጉ እየጨመረ በመምጣቱ ...

Read More »

በተለያዩ ከተሞችና ዩኒቨርስቲዎች ተቃውሞው እንደቀጠለ ነው

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 4/2010) በተለያዩ ከተሞችና ዩኒቨርስቲዎች ተቃውሞዎች ሲደረጉ መዋላቸው ተገለጸ። የአጋዚ ሰራዊት ዛሬም ግድያ ፈጽሟል። ህዝቡ ደግሞ በአምቦ ሁለት የአጋዚ ወታደሮችን መግደሉ ታውቋል። በጨለንቆ ከትላንት በስቲያ የተደረገውን ጭፍጨፋ በመቃወም በበርካታ ከተሞች ተቃውሞዎች ተካሂደዋል። በሰሜን ወሎ ኡርጌሳ ትላንት የጀመረው ተቃውሞ ቀጥሎ 3 ሰዎች የተገደሉ ሲሆን ህዝቡ በቁጣ አንድ ከባድ ተሽከርካሪ መሰባበሩ ታውቋል። በደብረታቦር ዩኒቨርስቲ የአጋዚ ሰራዊት ተማሪዎች ላይ በመተኮስ ግድያ መፈጸሙን ...

Read More »

ትራምፕ የኦባማን ላይብረሪ መጸዳጃ ቤት ለማጽዳት እንኳን ብቁ አይደሉም ተባለ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 4/2010) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የኦባማን ላይብረሪ መጸዳጃ ቤት ለማጽዳት እንኳን ብቁ አይደሉም ሲል በአሜሪካ የሚታተም አንድ ታዋቂ ዕለታዊ ጋዜጣ በርዕሰ አንቀጹ አሰፈረ። ዩ ኤስ ኤ ቱደይ የተሰኘው ይህ ጋዜጣ ጠንከር ያለ ትችት በመሰንዘር የሚታወቅ ጋዜጣ ባይሆንም ትላንት ማክሰኞ ይዞ የወጣው ርዕሰ አንቀጽ ግን በአሜሪካ በሚገኙ ሌሎች መገናኛ ብዙሃን መነጋገሪያ ሆኗል። የጉዳዩ መነሻ የሆነው የፕሬዝዳንት ትራምፕ ትላንት በቲውተር ...

Read More »

የጋምቤላ ክልል እዳውን ከፍሎ ጨረሰ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 4/2010) የጋምቤላ ክልል ለ10ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በአል ከፌደራል መንግስት የተበደረውን የ346 ሚሊየን ብር ብድር በብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ ሆኖ መክፈሉ አስታወቀ። ክልሉ ብድሩን ይክፈል እንጂ አሁንም በክልሉ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን የክልሉ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ጠቁሟል። ክልሉ ባለፈው መስከረምና ጥቅምት ለመንግስት ሰራተኞች በወቅቱ ደሞዝ መክፈትል አቅቶት በርካታ ችግሮች መፈጠራቸውን ኢሳት በወቅቱ ባቀረበው ዘገባ አመልክቶ ነበር። የብሔር ብሔረሰቦች ...

Read More »

የሕወሃት መሪዎች የአሜሪካንን ሽምግልናና ድጋፍ ይጠይቁ ተባለ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 4/2010) በኢትዮጵያ ሕግና ስርአት ሙሉ በሙሉ ከመፍረሱ በፊት የሕወሃት መሪዎች የአሜሪካንን ሽምግልናና ድጋፍ እንዲጠይቁ አንድ የአሜሪካ የቀድሞ ዲፕሎማት ጥሪ አቀረቡ። ሀገሪቱን ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርአት ለመውሰድና ሁሉም ፓርቲዎች የሚሳተፉበት ጉባኤ ለማካሄድ የአሜሪካንን አደራዳሪነትና ሽምግልና ሕወሃት እንዲጠይቅ ሀሳብ አቅርበዋል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር የነበሩት አምባሳደር ኽርማን ኮህን በማህበራዊ ገጻቸው ትላንት ባሰራጩት አጭር መልዕክት የሕወሃት መሪዎች ሁሉ ...

Read More »

የህወሃት አገዛዝ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን ዘጋ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 4/2010) በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች የተነሳውን ህዝባዊ አመጽ ተከትሎ የህወሃት አገዛዝ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን መዝጋቱ ታወቀ። ፌስቡክና ትዊተርን የመሳሰሉት ማህበራዊ ድረ ገጾች ዝግ መሆናቸው ታውቋል። ወትሮም ደካማ የነበረው የኢትዮጵያ የኢንተርኔት አገልግሎት አሁን ላይ ጭራሹኑ የፌስ ቡክና ትዊተር ድረገጾች እንዲዘጉ ሲደረግ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ የወጡ መረጃዎች እንዳይሰራጩ ለማድረግ መሆኑ ታውቋል። በአዲግራት ዩኒቨርስቲ ዜጎች መገደላቸው በተለይ ...

Read More »

የህግ የበላይነትን ማስከበር ያለበት ሃይል የኦሮሞ ህዝብን መግደሉ ተቀባይነት የለውም ተባለ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 4/2010) የህግ የበላይነት ማስከበር ያለበት ሃይል የኦሮሞ ህዝብን መግደሉ ተቀባይነት እንደሌለውና ለህግ እንደሚቀርብ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ገለጹ። ጉዳቱን ያደረሰው ሃይል ማን እንደጠራውና በማን ትዕዛዝ ቦታው ላይ እንደተገኘ አላወቅንም ብለዋል። ሰሞኑን በምስራቅ ሀረርጌ ዞን ሜታ ወረዳ ጨለንቆ ከተማ በሕወሃት የጦር አዛዦች የሚመራው ወታደራዊ ሃይል 18 ሰዎችን መግደሉንና በርካቶችን ማቁሰሉ ተዘግቧል። ይህንን ግድያ ተከትሎ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ...

Read More »

በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የተጀመረው ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 3/2010) በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የተጀመረው ተቃውሞ መቀጠሉ ታወቀ። በወልዲያ፣ በጎንደር፣ በባህርዳርና በደብረታቦር ዩኒቨርስቲዎች የተማሪዎች ተቃውሞ በመካሄድ ላይ ነው፡፡ የአጋዚ ሰራዊት በዩኒቨርስቲዎቹ ግቢ በመግባት ተማሪዎችን በመደብደብ ላይ መሆኑንም የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ሻምቡ ግቢ ሁለት ተማሪዎች ተገድለዋል። በአምቦ ዩኒቨርስቲ ተማሪው የአቋም መግለጫ በማውጣት ትምህርት ማቆሙን አስታውቋል። የህወሃት አገዛዝ ደጋፊ የሆኑ አክቲቪስቶች መንግስት ዩኒቨርስቲዎችን እንዲዘጋ ግፊት እያደረጉ መሆኑም ተሰምቷል። በአጠቃላይ ...

Read More »

ተቃውሞ በተለያዩ ከተሞች እንደቀጠለ ነው

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 3/2010) በኢትዮጵያ የሕወሃት አገዛዝ ከስልጣን እንዲወርድ የሚካሄደው ተቃውሞ በተለያዩ ከተሞች መቀጠሉ ተነገረ። በሀገሪቱ የተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ተማሪዎች በመገደላቸው ተቃውሞው በተለያዩ ከተሞች እንዲባባስ ምክንያት ሆኗል። የሕወሃት አጋዚ ወታደሮች ተቃውሞዎቹን ለመቆጣጠር እንደተሳናቸውም ምንጮቻችን ገልጸዋል። በቋንቋና ብሔር ላይ የተመሰረተው የሕወሃት ፌደራሊዝም ውጤቱ ግጭትና ትርምስ መሆኑን እያመላከተ ይገኛል። ግጭቶችና ጥቃቶች አንዴ በስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች ሌላ ጊዜ ደግሞ በዩኒቨርስቲዎች የሚከሰቱት ብሔርን ከብሔር በመለየትና ቋንቋን ...

Read More »

በስደተኞች ጉዳይ የአውሮፓ መንግስታት ተባባሪዎች ናቸው በሚል ተከሰሱ

(ኢሳት ዜና–ታህሳስ 3/2010) አምንስቲ ኢንተርናሽናል በሊቢያ በአፍሪካ ስደተኞች ላይ እየተካሄደ ላለው ሰቆቃ የአውሮፓ መንግስታት ተባባሪዎች ናቸው ሲል ከሰሰ። የሰብአዊ መብት ድርጅቱ ዛሬ ባወጣው ሪፖርት የአውሮፓ መንግስታት በስደተኞቹ ላይ ለሚፈጸመው ሰቆቃ በተግባር ተሳታፊ ናቸው ብሏል። አምንስቲ ኢንተርናሽናል እንዳወጣው ሪፖርት ከሆነ የአውሮፓ መንግስታት ስደተኞቹ ባህር አቋርጠው እንዳይመጡባቸው እዛው ሊቢያ ውስጥ ታግተው እንዲቆዩ ለአዘዋዋሪዎች፣ለታጣቂዎችና ለሊቢያ ተቋማት ገንዘብ ይሰጣሉ። በዚህም ምክንያት ይላል የድርጅቱ መግለጫ ...

Read More »