.የኢሳት አማርኛ ዜና

በረከት ስምዖን ህወሃትን ለመታደግ እየተንቀሳቀሱ ነው ተባለ

በረከት ስምዖን ህወሃትን ለመታደግ እየተንቀሳቀሱ ነው ተባለ (ኢሳት ዜና ግንቦት 14 ቀን 2010 ዓ/ም) ዶ/ር አብይ አህመድ ጠ/ሚኒስትር ሆኖ መመረጡን ያልተቀበሉት አቶ በረከት ስምዖን፣ ከህወሃት ጋር በመሆን የእነ ዶ/ር አብይንና ለማን ቡድን ለመምታት እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኝ ምንጮች ገልጸዋል። በኢሃዴግ ውስጥ ያላቸው ተቀባይነት እየተመናመነ የመጣው አቶ በረከት፣ በድርጅት አባልነት ከተመዘገቡበት ብአዴን ይልቅ ከህወሃት ጋር ጥምረት በመፍጠር እርሳቸውና በህወሃት ዙሪያ የሚገኙ ጓደኞቻቸው የሚቆጣጠሩትን ...

Read More »

ኢትዮጵያ በሆላንድ ኢምባሲ ልትከፍት ነው

ኢትዮጵያ በሆላንድ ኢምባሲ ልትከፍት ነው (ኢሳት ዜና ግንቦት 14 ቀን 2010 ዓ/ም) የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምንጮች እንደገለጹት ኢትዮጵያ ሆላንድ ዘ ሄግ ከተማ ላይ ኢምባሲ ለመክፈት በዝግጅት ላይ ናት። የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት አባይ ወልዱ በምባሳደርነት ተሹመው እንደሚመጡ ታውቋል። አቶ አባይ ከህወሃት ሊ/መንበርነትና ከትግራይ ክልል ርዕሰ ብሄርነት ከተነሱ በሁዋላ በአምባሳደርነት እንደሚሾሙ የታወቀ ቢሆንም፣ የት አገር እንደተመደቡ አልታወቀም ነበር። የውጭ ጉዳይ ምንጮች ...

Read More »

በሽንሌ ዞን የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ ለተጎዱ ሰዎች እርዳታ አለመላኩን የአካባቢው ተወላጆች ተናገሩ

በሽንሌ ዞን የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ ለተጎዱ ሰዎች እርዳታ አለመላኩን የአካባቢው ተወላጆች ተናገሩ (ኢሳት ዜና ግንቦት 14 ቀን 2010 ዓ/ም) ሰሞኑን በኢትዮ-ሶማሊ ክልል በሽንሌ ዞን ፣ በሃርዋ ፣ ገሚ፣ አይሎሶና ሌሎችም ቦታዎች አውሎ ንፋስ ቀላቅሎ የጣለውን ዝናብ ተከትሎ የተጎዱ ዜጎች እስካሁን ድጋፍ ያልተደረገላቸው በመሆኑ ለችግር ተዳርገዋል። በርካታ ቁጥር ያላቸው ቤቶች መፍረሳቸውን፣ አንድ ሺ የሚሆኑ የእርሻ ማሳዎች በጎርፍ መወሰዳቸውን የአካባቢው ተወላጆች ...

Read More »

በአርቢትር ኢያሱ ፈንቴ ላይ ድብደባ በመፈጸማቸው ቅጣጥ ከተጣለባቸው የወልዋሎ ተጫዋቾእች መካከል የአምስቱ ቅጣት እንዲነሳ ተደረገ።

በአርቢትር ኢያሱ ፈንቴ ላይ ድብደባ በመፈጸማቸው ቅጣጥ ከተጣለባቸው የወልዋሎ ተጫዋቾእች መካከል የአምስቱ ቅጣት እንዲነሳ ተደረገ። (ኢሳት ዜና ግንቦት 14 ቀን 2010 ዓ/ም) ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ-ከመከላከያ ጋር ባደረገው ጨዋታ ላይ የመሀል ዳኛ ኢያሱ ፈንቴ የሰጡትን ውሳኔ በመቃወም የወልዋሎ ተጫዋቾችና የቡድን መሪው ዳኛውን መሀል አስገብተው የፈጸሙት ድብደባ ብዙዎችን ማሳዘኑና ማነጋገሩ ይታወሳል። ድርጊቱን ተከትሎ “ዳኞች ዋስትና ካልተሰጠን ዳግም አናጫውትም”፡በማለታቸው ፕሪሚየር ሊጉ ለተወሰነ ጊዜ ...

Read More »

የዋልያ ቢራ ሰራተኞች የስራ ማቆም አድማ አደረጉ

የዋልያ ቢራ ሰራተኞች የስራ ማቆም አድማ አደረጉ (ኢሳት ዜና ግንቦት 13 ቀን 2010 ዓ/ም) በሆላንዱ ታዋቂ የቢራ ፋብሪካ ሃይነከን የተገነባው ቂሊንጦ በሚገኘው የቢራ ፋብሪካ ውስጥ በመጫንና በማውረድ ስራ ላይ የተሰማሩ ከ500 የማያንሱ ሰራተኞች መብታችን አልተከበረልንም በሚል የስራ ማቆም አድማ አድርገዋል። አድማው ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በመካሄድ ላይ ሲሆን፣ በፋብሪካው የተመረቱ የቢራ ምርቶች ሳይሰራጩ ቀርተዋል። ሰራተኞቹን በኮንትራት የሚያሰራቸው ኤዶምያስ ኢንተርናሽናል ሃላፊነቱ የተወሰነ ...

Read More »

ኢትዮጵያ ብድር የመክፈል አቅሟ በመዳከሙ የአጭር ጊዜ ብድር መውሰድ አቆመች

ኢትዮጵያ ብድር የመክፈል አቅሟ በመዳከሙ የአጭር ጊዜ ብድር መውሰድ አቆመች (ኢሳት ዜና ግንቦት 13 ቀን 2010 ዓ/ም) ኢትዮጵያ ባጋጠማት የውጭ ምንዛሬ እጥረት የተነሳ የተበደረችውን ብድር በወቅቱ ለመክፈል አቅሟ እየተዳከመ መምጣቱን ተከትሎ በአጭር የክፍያ ጊዜና በከፍተኛ የወለድ መጠን የሚሰጡ ብድሮችን መበደር ማቆሟን የገንዘብ ሚኒስትሩ ለሪፖርተር ተናግረዋል። አገሪቱ ወደ ውጭ ከምትልካቸው ምርቶች በቂ የሆነ የውጭ ምንዛሬ ታገኛለች ተብሎ ቢታቀድም እቅዱ ሊሳካ አለመቻሉን ...

Read More »

የወሎ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በውሃ ችግር ምክንያት የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

የወሎ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በውሃ ችግር ምክንያት የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ (ኢሳት ዜና ግንቦት 13 ቀን 2010 ዓ/ም) የኮምቦልቻ ግቢ ተማሪዎች ዛሬ ግንቦት 13 ቀን 2010 ዓም በሰልፍ በመውጣት የውሃ ችግራቸው እንዲቃለል ጠይቀዋል። ተማሪዎቹ ካለፉት 2 ሳምንታት ጀምሮ የሚጠጣ ውሃ እንኳን በበቂ ሁኔታ ማግኘት አልቻሉም። ተማሪዎቹ ችግራቸውን ለተለያዩ ባለስልጣናት ቢያመለክቱም መልስ የሚሰጣቸው አካል አላገኙም። የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ተገኝተው ተማሪዎችን ለማረጋጋት ...

Read More »

የአማራ ክልል ኢንቨስትመንት በማስፈጸም ረገድ በርካታ ፈተናዎች እንዳጋጠሙት ተገለጸ፡፡

የአማራ ክልል ኢንቨስትመንት በማስፈጸም ረገድ በርካታ ፈተናዎች እንዳጋጠሙት ተገለጸ፡፡ (ኢሳት ዜና ግንቦት 13 ቀን 2010 ዓ/ም) የማስፈጸም ችግሩ በአንድ ሴክተር መስሪያ ቤት ብቻ ሳይሆን በሁሉም ሴክተሮቻችን የሚታይ ችግር ነው የሚሉት የአማራ ክልል ከፍተኛ ባለስልጣን አብዛኛውን ነገር እያሰረ ያለው የማስፈጸሙ ችግር እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ከኢንቨስትመንት አኳያ ባለሃብት መማምጣት ላይ ችግር እንደሌለ ሚገልጹት ከፍተኛ አመራር ዋናው ችግር የመጡትን ባለሃብቶች በመጡበት ፍጥነት ወደ ስራ ...

Read More »

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የተቀሰቀሰው የኢቦላ ቫይረስ እየተስፋፋ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 10/2010) በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የተቀሰቀሰው የኢቦላ ቫይረስ ወደ ሌሎች የሃገሪቱ የገጠር ከተሞች እየተስፋፋ መሆኑ ተሰማ። እስካሁን በቫይረሱ 45 ሰዎች መጠቃታቸው ታውቋል።የሌሎች 25 ሰዎች አሟሟትም ምናልባት ከቫይረሱ ጋር ሳይያያዝ አይቀርም በሚል አስከሬናቸው ላይ ምርመራ እየተደረገ መሆኑ ታውቋል። እንደዘገባው ከሆነ ቫይረሱ ወደ ገጠር ከተማዋ ማባንዳካ መዛመቱ በአንድ ሰው ላይ ምልክቱ መታየቱ ተሰምቷል። ከተማዋ አንድ ሚሊየን ያህል ሕዝብ የሚኖርባት መሆኑ ደግሞ ...

Read More »

ለደቡብ ሱዳን ተወላጆች ኢትዮጵያዊ ዜግነት ሊሰጥ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 9/2010) በመቶ ሺዎች ለሚቆጠሩ የደቡብ ሱዳን ተወላጆች ኢትዮጵያዊ ዜግነት ለመስጠት መወ ሰኑ ተቃውሞ አስነሳ። የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት በፌደራል መንግስቱ የተደረሰውን ስምምነት ለማስፈጸም ውሳኔ ማሳለፉ ታውቋል። ለደቡብ ሱዳናውያን በጅምላ የኢትዮጵያ ዜግነት እንዲሰጣቸው የተወሰነበት ይፋዊ ምክንያት አልተገለጸም። የጋምቤላ የመብት ተሟጋቾች ዜግነት የሚሰጣቸው ደቡብ ሱዳናውያን ቁጥራቸው 400ሺህ እንደሚጠጋ ይገልጻሉ። የኢትዮጵያውያን አኝዋኮችን ህልውና ለማጥፋት የሚደረገውን ሚስጥራዊ እንቅስቃሴ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያስቆም የመብት ...

Read More »