ኢሳት ዜና:- ኢሳት በቅርቡ የከፈተው የአጭር ሞገድ ስርጭት በኢትዮጵያ መንግስት መታፈን መጀመሩን ተከትሎ የሳተላይት የሬዲዮ ስርጭት በመጀመር የመንግስትን አፈና ለመቋቋም ወሳኝ እርምጃ ወስዷል። የአጭር ሞገድ ስርጭቱ እየታፈነም ቢሆን እንደሚቀጥል የገለጠው ማኔጅመንቱ፣ አሁን ደግሞ ኢትዮጵያውያን በሳተላይት ኢሳትን የሚስቡበት አማራጭ ቀርቦላቸዋል። አዲሱ የሳተላይት ስርጭት በ ኤቢ 2 ሳተላይት፣ በስምንት ዲግሪ ዌስት በ11 ሺ 5 መቶ 95 ሞገድ ቨርቲካል በ27 ሺ 5 መቶ ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴለቪዥን (ኢሳት) የገንዘብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ዘመቻ
ጥቅምት 20 ቀን 2004 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴለቪዥን (ኢሳት) ከህዳር እስከ ጥር ወር 2004 ዓ.ም ለሚያደረገው የገንዘብ ድጋፍ ማሰባሰቢያ ዘመቻ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ፣ http://www.ethsat.com/esat_international_fund_raising_campaign/ በሃገራች በሥልጣን ላይ ያለው አገዛዝ የኢትዮጵያን ህዝብ በመረጃ ጨለማ ውስጥ በማቆየት የግዛት ዘመኑን ለማራዘም የዘረጋውም የአፈና ቀንበር ለመስበርና፣ ነጻነት፣ ፍትህና ዴሞክራሲን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ፣ የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴለቪዥን የበኩሉን አስተጽዖ ሲያደርግ ቆይቷል። በአሁኑ ጊዜ ኢሳት የተቋቋመበትን ...
Read More »“የኢህአዴግ ስርዓተ-መንግስት ሳይውል ሳይድር በዲሞክራሲያዊ ስርዓት መተካት አለበት” ሲል የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዶሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ገለፀ
ኢሳት ዜና:- መድረክ ይህን ያለው፦ “በኢትዮጵያ ድርቅ አለ፤ ረሀብም አለ፤ ኢኮኖሚውም መንግስት እንደሚለው እያደገ አይደለም። የፖለቲካ ምህዳሩም ከመቼውም ጊዜ በላይ ጠቧል” በሚል ርዕስ ትናንት ባወጣው ባለ ስምንት ገፅ መግለጫ ላይ ነው። ፕሬዚዳንት ግርማና ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ለፓርላማ ባቀረቡት የአዲስ አመት ንግግር ሰፋፊ ዲስኩሮችን አስደምጠውናል ያለው መድረክ፤በንግራቸው የነካኳቸው ጉዳዮች ብዙ ቢሆኑም በሁሉም ዘርፎች ያሏቸው ነገሮች ስህተት እንደሆኑ መረጃዎችን በመጥቀስ አብራርቷል። በአለም ...
Read More »በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሻማ ማብራት ሥነ-ሥርዐት ሊያደርጉ ነው
ኢሳት ዜና:- በአሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በእስር ላይ የሚገኙ ጋዜጠኞችና የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች እንዲፈቱ ለመጠየቅ በኋይት ሀውስ ፊት ለፊት የሻማ ማብራት ሥነ-ሥርዐት ሊያደርጉ ነው:: ማርች ፎር ፍሪደም ለኢሳት በላከው መግለጫ ላይ እንዳመለከተው ኢትዮጵያኑ ኖቪምበር 6 በኋይት ሀውስ ለፊት ከ6ፒኤም ጀምሮ የሻማ ማብራት ሥነ-ሥርዐት በማድረግ በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞች እንዲፈቱና የኦባማ አስተዳዳር በመለስ ዜናዊ አገዛዝ ላይ ጫና እንዲያሳርፉ ይጥይቃሉ። በስነስርአቱ ላይ ...
Read More »በአርባ ምንጭ በተነሳው ውዝግብ የታሰሩ 28 ሰዎች አለመለቀቃቸው ታወቀ
ኢሳት ዜና:-ግለሰቦቹ የታሰሩት አካባቢውን ህዝብ ለአድማ ለማነሳሳት ሙከራ አድርጋችሁዋል ተብለው ነው። ግለሰቦቹ ከዚህ ቀደም የመንግስት ባለስልጣናት የአካባቢውን ደን በመመንጠር ሰፋፊ ቤቶችን ለግል የመኖሪያ ቤቶች ግንባታ አውለዋል በሚል መታሰራቸው ይታወቃል። እስረኞቹ አቤቱታቸውን እስከ ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ድረስ ቢያቀርቡም ሰሚ አጥተው ከቆዩ በሁዋላ፣ የአካባቢው ባለስልጣናት ለምን አጋላጣችሁን በሚል ሰብስበው ማሰራቸው ታውቋል። ምንም እንኳ ግለሰቦቹ ያቀረቡት አቤቱታ መንግስት ዘግይቶም ቢሆን ትክክል ነው ቢልም ፣ ...
Read More »በዋካ ከተማ የፌደራል ፖሊስ አሁንም ከተማውን በመቆጣጠሩ ለአራተኛ ቀን ህዝቡ እንደልቡ አንዳይንቀሳቀስ መደረጉን ዘጋቢያችን ገለጠ
ኢሳት ዜና:-ባለፈው ማክሰኞ በደቡብ ክልል በዳውሮ ዞን የዋካ ከተማና አካባቢው ህዝብ ከመብት ጥያቄዎች ጋር በተያያዘ ያነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ የፌደራል ፖሊስ አንድም ሰው በመንገድ ላይ እንዳይንቀሳቀስ በመከልከሉ ከተማው ጭር ብሎ መዋሉን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጠዋል። ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንደሌላ፣ ተምህርትቤቶች እና ሌሎች የአገልግሎት መስጫ ተቋማት መዘጋታቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል። በስፍራው ተገኝቶ መረጃዎችን በመሰብሰብ ላይ የሚገኘው የደቡብ ተወካያችን እንዳለው፣ በፖሊስ ጣቢያ የነበሩት አገር ...
Read More »በደቡብ ክልል በዳውሮ ዞን የዋካ ከተማና አካባቢው ህዝብ ከመብት ጥያቄዎች ጋር በተያያዘ ያነሳው ተቃውሞ ለሶስተኛ ቀን እንደቀጠለ ነው
ኢሳት ዜና:-ባለፈው ማክሰኞ ከወረዳና ከልማት ጋር በተያያዘ የተነሳው ተቃውሞ በቀጠለበት ሰአት የፌደራል ፖሊስ ማንኛውም ሰው በከተማው ሲንቀሳቀስ ቢገኝ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል። በሺ የሚቆጠሩ የፌደራልና የክልሉ ፖሊስ አባላት በከተማው ዋና ዋና መንገዶችና ማህበራዊ አገልግሎት መስጪያ ተቋማት ላይ ጥበቃ በማድረግ ህብረተሰቡ በነጻነት እንዳይንቀሳቀስና ቤቱ ውስጥ እርፎ እንዲቀመጥ እያስፈራሩ ነው። በስፍራው ተገኝቶ መረጃዎችን በመሰብሰብ ላይ የሚገኘው የደቡብ ተወካያችን እንዳለው፣ የክልሉና የፌደራል ባለስልጣናት ህዝቡ ...
Read More »የኢትዮጵያ አርቲስቶች በቅርቡ ወደ ሕንድ ዴሊ በመጓዝ ያሳዩትን ትርዒት ተከትሎ የቀረበ ዘገባ ውጥረት ማስከተሉን ታወቀ
ለውዝግቡ መነሻ የሆውን እና የኢትዮጵያውያንን ስሜት የሚጎዳውን ጽሁፍ ያተመው ዘ ታይምስ ኦፍ ኢንድያ ጋዜጣ ዘገባውን እንዲያርም፣የኢትዮጵያ ኤምባሲም ማስተባበያ እንዲሰጥ በህንድ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ጠይቀዋል። በህንድ የሚማሩ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን ያስቆጣው ዘገባ፣ በዘ ታይምስ ኦፍ ኢንድያ ኦክቶበር 20/2011 የወጣው እትም ነው። ለዘገባው መነሻ የሆነው ከኦክቶበር 15 እስከ 21/2011 የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቲያትር የባህል ቡድን በኢንዲያን ኢንተርናሽናል ሴንተር ያሳየው የሙዚቃ ትርኢት ነው፤ ይህንን የሙዚቃ ...
Read More »በደቡብ ክልል በዳውሮ ዞን የዋካ ከተማና አካባቢው ህዝብ ከመብት ጥያቄዎች ጋር በተያያዘ ያነሳው ተቃውሞ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው
ኢሳት ዜና:- ማክሰኞ እለት ከወረዳና ከልማት ጋር በተያያዘ የተነሳው ተቃውሞ ሌሊቱን በሙሉ አድሮ በማግስቱም ተጠናክሮ መቀጠሉን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመልክቷል። የአካባቢው እና የክልሉ ፖሊስ ሁኔታውን መቆጣጠር ባለመቻላቸው በ7 መኪና የተጫኑ የፌደራል ፖሊስ አባላት በስፍራው ተገኝተዋል። የክልሉና የፌደራል ባለስልጣናትም በአካባቢው ተገኝተዋል። እስካሁን ድረስ ከ26 አላነሱ ሰዎች ተይዘው መታሰራቸውንና 4 ግለሰቦችም ተደብድበው መታሰራቸውን ለማወቅ ተችሎአል። ከተሳሩት መካከል አቶ አድነው ማሞ፣ ተፈራ ታደሰ ...
Read More »የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ከሀላፊነታቸው የተነሱት፦”ብቃት ስለሌላቸው” ነው ሲሉ የመንግስት መገናኛ ብዙሀን ዘገቡ
ኢሳት ዜና፡- ብአዴኖች በህወሀት ክፍፍል ወቅት ለአቶ መለስ ቡድን ታማኝነታቸውን በማሳየታቸው ምክንያት በሹመት በተንበሸበሹበት ወቅት ነው- የብአዴኑ አቶ ከፍያለው አዘዘ- ከመንግስት ጋዜጠኝነት ተነስተው የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ሆነው የተሾሙት። ለረዥም ጊዜ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ሥራ አስኪያጅ ሆነው የቆዩት አቶ ከፍያለው አዘዘ በአቶ ኩማ ደመቅሳ የሚመራው ካቤኔ አዲስ አበባን ማስተዳደር ሲጀምር የከተማዋ ምክትል ከንቲባ ሆነው ተመደቡ። ይሁንና አቶ አዲሱ ለገሰን፣ ...
Read More »