ታሪካዊው “መስቀል ፍላወር” ሆቴል እንዲፈርስ ተወሰነ

ጥር ፳፰(ሃያ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፎርቹን ሳምንታዊ ጋዜጣ እንደዘገበው፤ ሆቴሉ የሚፈርሰው በአካባቢው  ለሚሰራ የ 3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መንገድ ፕሮጀክት ተብሎ ነው። የ3 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር መንገዷን ለመስራት 400 ሚሊዮን ብር  ያስፈልጋል መባሉንም ጋዜጣው አስነብቧል። ሆቴሉ ለልማት ፕሮግራም ተብሎ  እንዲፈርስ  ከአስር ቀን በፊት በቂርቆስ ክፍለ-ከተማ ትዕዛዝ መውጣቱ ተመልክቷል። ባለፈው ስርዓት  የመንግስት እንዲሆን ተደርጎ በዋቢ ሸበሌ  ሆቴሎች ...

Read More »

ለህውሃት 40ኛ አመት መታሰቢያ ድግስ  ከባለሀብቶች ብቻ 45 ሚልየን ብር ተገኘቷል፡፡

ጥር ፳፯(ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በህዝባዊ ወያነ ሃርነት ትግራይ(ህወሀት)  ጽ/ቤት በተሰጠው መግለጫ  እንደተመለከተው፤ የካቲት 11 ለሚከበረው የድርጅቱ 40ኛ ዓመት በዓል ማክበሪያ   ከባለሀብቱ ብቻ  45 ሚልዩን ብር  ስፖንሰር ተገኝቷል፡፡ በመግለጫው በመቀሌ ከፍተኛ ተራራ ላይ የመለስን  ምስል የያዘ ባለሁት አውታር  ሐውልት እየተገነባ እንደሆነ የተጠቀሰ ሲሆን፤  የዚህም ወጪ  ከመቀሌ ዩኒቨርስቲ አና ከገጠር መንገዶች ተቋራጭ ድርጅት ይሸፈናል ተብሏል፡፡ እስካሁን በአዲስ አበባ ...

Read More »

በብአዴን  ወስጥ በተፈጠረ አለመግባባት የድርጅቱ መስራች ታደሰ ካሳ በምሬት ማልቀሳቸው ተሰማ

ጥር ፳፯(ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የብሔረ አማራ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ(ብአዴን ) ፤የድርጅቱን የትግል ጉዞ የሚተርክ  አዲስ መፅሃፍ አስጽፎ የድርጅቱ መስራች በሆኑትና በቅጽል ስማቸው <<ጥንቅሹ>>ተብለው በሚጠሩት   በአቶ ታደሰ ካሳ  እያስገመገመ  ሲሆን፤ በመጽሀፉ ይዘት ላይ በአመራሮቹ መካከል ላይ ከፍተኛ አለመግባባት ተፈጥሯል። በግምገማው ላይ  የብአዴን መስራች አይደለህም የተባሉት ታደሰ ካሳ፤ << ለላፉት 30 ዓመታት የማላውቀው ታሪክ ነው የተነገረኝ>> ሲሉ  በንዴት  ተናግረዋል። ...

Read More »

የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሩ በደረሰባቸው ድብደባና መድሀኒት ክልከላ ህይወታቸው አለፈ

ጥር ፳፯(ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የ9ኙ ፓርቲዎች በጠራው የአዳር ሰልፍ ታስረው የነበሩት  የመቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ በእስር ቤት ሳሉ በደረሰባቸው ድብደባና መድሀኒት ክልከላ ህይወታቸው ማለፉን ነገረ-ኢትዮጰያ ዘገበ የመላው አማራ አንድነት ድርጅት ምክትል ጸሀፊ የሆኑት መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ የህዳር 27/28 የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር በጠራው የአዳር ሰልፍ ላይ  ነው ክፉኛ  የተደበደቡት። የስኳር ህመምተኛ የሆኑት  የመአህድ ምክትል ጸሀፊ ከደረሰባቸው ...

Read More »

የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሩ በደረሰባቸው ድብደባና መድሀኒት ክልከላ ህይወታቸው አለፈ

ጥር ፳፯(ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የ9ኙ ፓርቲዎች በጠራው የአዳር ሰልፍ ታስረው የነበሩት  የመቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ በእስር ቤት ሳሉ በደረሰባቸው ድብደባና መድሀኒት ክልከላ ህይወታቸው ማለፉን ነገረ-ኢትዮጰያ ዘገበ የመላው አማራ አንድነት ድርጅት ምክትል ጸሀፊ የሆኑት መቶ አለቃ ተሰማ ወንድሙ የህዳር 27/28 የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር በጠራው የአዳር ሰልፍ ላይ  ነው ክፉኛ  የተደበደቡት። የስኳር ህመምተኛ የሆኑት  የመአህድ ምክትል ጸሀፊ ከደረሰባቸው ...

Read More »

የህዝብና የመንግስት የልማት ድርጅቶች፤ የባለስልጣናት መሸሸጊያ ናቸው ተባለ

ጥር ፳፯(ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-<<በየክልሉ የሚገኙ የህዝብና የመንግስት የልማት ድርጅቶች፤ የባለስልጣናት መሸሸጊያ ናቸው>> ሲል የመንግስት ኮሙነኬሺን ቢሮ ባሰባሰበው የምርጫ ድጋፍ የህዝብ አሰተያየት አመለከተ፡፡ በልማት ድርጅት ስም የብአዴን፣የህወሀትና  የኦህዴድ ንብረቶች በሆኑት እነኚህ ድርጅቶች ላይ ለስራ የሚመድቡት በ አመዛኙ በየድርጅቶቹ ውስጥ ጥፋት ፈጽመው እርምጃ ይሚወሰድባቸው የድርጅት አባላት መሆናቸውን ያመለከተው የኮሙኒኬሽን ቢሮ፤ ድርጅቶቹ የሙሰኛ ባለስልጣናት መሸሸጊያ ዋሻ መሆናቸውን አመልክቷል። የህወሀቱ ...

Read More »

መምህራን በፖለቲካ መስፈርት እየተሰጠ ያለን እድገት ተቃወሙ

ጥር ፳፯(ሃያ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ለሚገኙ ለአንዳንድ አንደኛና መለስተኛ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የወጣው የደረጃ እድገት ማስታወቂያ በርካታ መምህራንን እንዳሳዘነ መምህራኑ ለኢሳት ገለጹ:: መምህራን እንዳሉት ለደረጃ እድገቱ እንደዋነኛ መስፈርት ሆነው የተቀመጡት፦ “በልማት ቡድንና በ1 ለ5 አደረጃጀቶች የሚያምን” ፣ ” በቡድኖቹ  በመሳተፍ ውጤት ያስመዘገበ”  የሚሉ  እና  ሌሎች ተመሳሳይ ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው ነጥቦች ናቸው። እነኚህ መስፈርቶች  ለመምህራን ...

Read More »

የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አባላት በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን ተቀላቀሉ

ጥር ፳፮(ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-<<ብሄራዊ ምርጫ ቦርድና ኢህአዴግ በወሰኑብን ፖለቲካዊ ውሳኔ ምክንያት አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን ተነጥቀናል>> ያሉ የአንድነት ፓርቲ አባላት› በይፋ ሰማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን ሰማያዊ ፓርቲ አስታውቋል፡፡ በእነ በላይ ፍቃዱ አመራርነት አንድነት ፓርቲን በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ሲመሩ የነበሩ አመራሮች ዛሬ ጥር 26 ቀን 2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ፤ ከቀድሞ ፓርቲያቸው አንድነት ጋር ...

Read More »

የዞን 9 ጦማሪዎች እና ጋዜጠኞች ሰብሳቢ ዳኛው ከችሎቱ እንዲነሱላቸው ጠየቁ

ጥር ፳፮(ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ላለፉት 9 ወራት በ እስር ላይ ይሚገኙት የዞን ዘጠኝ ጦማርያንና ጋዜጠኞች ሰብሳቢ ዳኛው ከችሎት እንዲነሱ ጠየቁ፡፡ ጦማርያኑና ጋዜጠኞቹ ለ17ኛ ጊዜ ጥር 26/2007 ዓ.ም  በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ልደታ ምድብ  ቸሎት ሲቀርቡ  በጽሁፍ ባቀረቡት አቤቱታ፦ የችሎቱ ሰብሳቢ ዳኛ የሆኑት አቶ ሸለመ በቀለ ...

Read More »

ሰደተኛ ኢትዮጰያውያን ቀይ ባህር ውስጥ ሰጠሙ

ጥር ፳፮(ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአመዛኙ  ኢትዮጵያውያን፣ ሶማሊያውያንና የአካባቢው ሀገራት ዜጎች እንደሆኑ የሚገመቱ  ስደተኞች ሲጓዙባት የነበረች አነስተኛ ጀልባ ቀይ ባህር ሰጠመች። <<ሳባ>>የተሰኘው የየመን መንግስት የዜና አገልግሎት ጀነራለ ሳሊህ አልሰብሪ የተባሉ የሀገሪቱን ባለስልጣናት  ዋቢ በማድረግ  እንደዘገበው   ስደተኞቹን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረችው ጀልባ  <<ታይዚ>>ተብላ ወደምትጠራው  የየመን ደቡባዊ ምእራብ  ግዛት ስታመራ  ነው በመጥፎ አየር ሳቢያ የሰጠመችው። በጀልባዋ ሲጓዙ ከነበሩት 49 ስደተኞች ...

Read More »