ድምጻችን ይሰማ የጠራው የሳንቲም መሰብሰብ ተቃውሞ  ተጀመረ

መጋቢት ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ወደ ማእቀብ እና ትብብር የመንፈግ  ሂደት መሸጋገሩን ድምጻችን ይሰማ ካስታወቀ በሁዋላ፣ አርብ መጋቢት 20 የሳንቲም መሰብሰቡ ሂደት ተጀምሯል። ምን ያክል ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ጥሪውን ተቀብለው ተግባራዊ እያደረጉት መሆኑን ለማወቅ አስቸጋሪ ቢሆንም ሙስሊሙ ከዚህ በፊት ይተላለፉ የነበሩ የድምጻችን ይሰማን መመሪያዎች ሲተገብር በመቆየቱ፣ አዲሱን መመሪያም ተግባራዊ ያደርጋል ተብሎ እንደሚታሰብ ዘጋቢያችን ገልጿል። የሳንቲም ...

Read More »

65 ኢትዮጵያውያን በኬንያ ፍርድ ቤት ቀረቡ

መጋቢት ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኬንያው  ዘ ደይሊ ኔሽን እንደዘገበው ኢትዮጵያውያኑ ወደ አገሪቱ በህገወጥ መንገድ በመግባታቸው እያንዳንዳቸው 2 መቶ ሺ ሽልንግ እንዲከፍሉ የኢሲዮሎ ፍርድ ቤት ወስኖባቸዋል። ሁሉ ም ስደተኞች ባለፈው ሰኞ ሳምቡሩ በተባለው ስፍራ ላይ የተያዙ ሲሆን፣ ተከሳሾች ያለፈቃድ ወደ ኬንያ መግባት እንደማይቻል ባለማወቃቸው ምህረት እንዲደረግላቸው ጠይቀዋል። ይሁን እንጅ ፍርድ ቤቱ የተጠቀሰውን ገንዘብ እንዲከፍሉ ወይም ለ3 ...

Read More »

በኦሮምያ ዋና ከተማ የውሃ ችግሩ ተባብሶ ቀጥሏል

መጋቢት ፲፰(አስራ ስምንት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአዳማ ከተማ ነዋሪዎች እንደሚሉት ከማሃል ወደ አዋሽ በሚወስደው መንገድ ላይ ያሉ አካባቢዎች ውሃ ካጡ ረጅም ጊዜ አስቆጥረዋል። ውሃ ጀሪካን በጋሪ ላይ ጭኖ መሄድ ወይም ለውሃ ወረፋ ረጃጅም ሰልፎችን መጠበቅ የእለት ተእለት ክስተት መሆኑን ነዋሪዎች ይገልጻሉ። በተመሳሳይም በትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቀሌ የሚታየው የውሃ ችግር ሊቀንስ አልቻለም። ኦሮምያን እመራለሁ የሚለው ኦህዴድም ሆነ ...

Read More »

9 ፓርቲዎች የጠሩት የተቃውሞ ሰልፍ በመጪው እሁድ ሊካሄድ ነው

መጋቢት ፲፯(አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪነት የተሰባሰቡትና ምርጫ ቦርድ ዕውቅና አልሰጠሁም በሚል ትብብራቸውን እንዲያቆሙ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ የሰጣቸው ዘጠኝ ፓርቲዎች በትብብር የጠሩት ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ የፊታችን እሁድ የአዲስአበባ እና የድሬዳዋ ከተሞችን ጨምሮ በአስራአምስት ዋና ዋና ከተሞች ይካሄዳል፡፡ ሆኖም አዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ከወዲሁ ሰልፉ በመንግስት በኩል ያልተፈቀደ ነው በሚል ለማጨናገፍ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በባህርዳር ...

Read More »

በኦሮሚያ እና ሌሎች አካባቢዎች የመጠጥ ውሃ ችግር ት/ቤቶችን ከማዘጋት አልፎ ለስደት እየዳረገ ነው

መጋቢት ፲፯(አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በመቶ ሚሊየን በሚገመት ወጪ በታላቅ ፌሽታ እያከበረ የሚገኘው የኦሮሞ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) አመራር በአንዳንድ የኦሮሚያ አካባቢዎች ትምህርት ቤቶችን እስከማዘጋት የደረሰውን የመጠጥ ውሃ ችግር ሊታደግ ያልቻለ መሆኑን መረጃዎች ጠቆሙ፡፡ ከግብርና ሚኒስቴር የወጣ አዲስ መረጃ እንደሚያሳየው፣ በኦሮሚያ ክልል አንዳንድ አካባቢዎች የተከሰተው የመጠጥ ውሃ ችግር ሕዝብን ለከፍተኛ ችግር ከመዳረጉም ...

Read More »

ድምጻችን ይሰማ ሳንቲም የመሰብሰብ  ተቃውሞ እንዲካሄድ ጥሪ አቀረበ

መጋቢት ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድምጻችን ይሰማ ባለፉት 3 ዓመታት የተካሄደው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ወደ ማእቀብ እና ትብብር የመንፈግ  ሂደት መሸጋገሩን ካስታወቀ በሁዋላ፣  ከመጋቢት 18፣2007 ዓም ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን ላልተወሰነ ጊዜ  ሳንቲምበመሰብሰብናበማጠራቀምራስላይየመቆጠብእቀባይፋ አድርጓል። በቅርቡ በቴሌላይተቃውሞ መደረጉን የገለጸው ድምጻችን ይሰማ፣  በሂደትም ከዚህ ከፍ ያሉ የትብብር መንፈግስልቶችንቀስበቀስወደመላመዱእናወደመተግበሩ፣ቀስበቀስምወደማሳደጉ መግባትተገቢሆኖእንዳገኘው ገልጿል። ድምጻችን ይሰማ ሳንቲም የመሰብሰብ እንቅስቃሴው  በሳንቲምዝውውሩላይእጥረትየሚፈጥር በመሆኑ መንግስት ህዝቡ ስልጣን ...

Read More »

በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የካሳ ክፍያ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ እንደሚዘረፍ ኦዲት መስሪያ ቤት አስታወቀ

መጋቢት ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የባለሰልጣኑ የኦዲት ሪፖርት እንደሚያሳየው በአማራ ክልል የባህርዳር ከተማ፣በምዕራብ ጎጃም ዞን የባህርዳር ዙሪያና የይልማና ዴንሳ ወረዳዎች የጣና- በለስ-ባህርዳር 400 ኪሎቮልት እና የባህርዳር- ደብረማርቆስ 400 ኪ.ቮ. የኃይልማስተላለፊያ ፕሮጀክቶች፣በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን የምስቃን ወረዳ፣በሀዲያ ዞን የሌሞ ወረዳ የወላይታ ሶዶ- አዲስ አበባ 400 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክት በካሳ ግምት ስም ከፍተኛ ገንዘብ ተበልቶባቸዋል። የጣና በለስ ...

Read More »

የሰማያዊ ፓርቲ የቅስቀሳ መልዕክቶች በመንግስት የመገናኛ ብዙሃን እንዳይተላለፉ እየተደረገ ነው

መጋቢት ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን መጋቢት 16/2007 ዓ.ም ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ፣ ከተላኩት የቅስቀሳ መልክቶች መካከል ” የመከላከያ ሰራዊቱ ሌሎችም የአገሪቱ ቁልፍ ተቋማት ከገዢው ፓርቲ ካድሬዎች ውጪ አልሆነም፣ በተለይም በገዛ ሃገራቸው ከስራ ይባረራሉ ፣ ተቋማቱን እውቀት የሌላቸው ካድሬዎች እንዲመሩት ተደርጓል፣ ገዢው ፓርቲ ፖሊስን፣ ሚዲያውን፣ መከላከያ ሰራዊቱን፣ ደህንነቱን ሰማያዊንና ሌሎች ተቃዋሚዎችን ለማጥፋት ሲጠቀምባቸው ቆይቷል የሚሉትና ሌሎችም ...

Read More »

“ኢህአዴግ የህዝቡ ብሶት አደጋ እንደሚያስከትል አውቋል” ስትል የአዲስ አበባ የኢህአዴግ የሴቶች ሊግ ም/ል ሊቀመንበር ተናገረች

መጋቢት ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሊጉ ም/ል ሊቀመንበር በመሆን ለአመታት ያገለገለችው ወ/ት እየሩሳሌም  አበረ  ከኢሳት ጋር ባደረገችው ቃለምልልስ “የአዲስ አበባ ህዝብ እንደሚገነፍል ድስት እፍ እፍ እየተባለ  ቢያዝም፣ አሁንም በርካታ የዲሞክራሲ እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን እያነሳ ነው” ብላለች። የታፈነ የመልካም አስተዳደር እና የዲሞክራሲ ጩኸት አለ የምትለው ወ/ት እየሩሳሌም፣ ገዢው ፓርቲም ህዝቡ በከፍተኛ ብሶት ላይ እንደሚገኝና አደጋ ሊያስከትል እንደሚችልም ...

Read More »

ኢትዮጵያ የአባይ ግድብ ግንባታን በየደረጃው የሚቆጣጠረውን ስምምነት ፈረመች

መጋቢት ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ በጋራ የፈረሙት አዲሱ ስምምነት ኢትዮጵያ በግድቡ ላይ በሙሉ ነጻነት የምትሰራውን ስራ እንደሚገድብ ከአረብኛ ወደ እንግሊዝኛ የተተረጎመው  ሰነድ አመልክቷል። ሰነዱ ኢትዮጵያ ግድቡን ለመገንባት በምታደርገው ማንኛውም እንቅስቃሴና በየትኛውም የግንባታ ደረጃ ላይ አለማቀፉ አጥኝ ቡድን ለሚሰጠው አስተያየት ተገዢ በመሆን እንድትተገብር ይገልጻል። አጥኝ ኮሚቴው የግድቡ ግንባታ የግብጽንና ሱዳንን የውሃ ድርሻ መጠን ይቀንሳል ወይም ...

Read More »