ድምጻችን ይሰማ ሳንቲም የመሰብሰብ  ተቃውሞ እንዲካሄድ ጥሪ አቀረበ

መጋቢት ፲፮(አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድምጻችን ይሰማ ባለፉት 3 ዓመታት የተካሄደው የሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ወደ ማእቀብ እና ትብብር የመንፈግ  ሂደት መሸጋገሩን ካስታወቀ በሁዋላ፣  ከመጋቢት 18፣2007 ዓም

ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን ላልተወሰነ ጊዜ  ሳንቲምበመሰብሰብናበማጠራቀምራስላይየመቆጠብእቀባይፋ አድርጓል።

በቅርቡ በቴሌላይተቃውሞ መደረጉን የገለጸው ድምጻችን ይሰማ፣  በሂደትም ከዚህ ከፍ ያሉ የትብብር መንፈግስልቶችንቀስበቀስወደመላመዱእናወደመተግበሩ፣ቀስበቀስምወደማሳደጉ መግባትተገቢሆኖእንዳገኘው ገልጿል።

ድምጻችን ይሰማ ሳንቲም የመሰብሰብ እንቅስቃሴው  በሳንቲምዝውውሩላይእጥረትየሚፈጥር በመሆኑ መንግስት ህዝቡ ስልጣን እንዳለው እንዲረዳ ያደርገዋል ብሎአል።

መንግስት ሳንቲምለማሰራትከፍተኛገንዘብየሚያወጣ በመሆኑ ፣ የሳንቲምዝውውሩማእቀብ ችግር እንደሚፈጥር የሚገልጸው ድምጻችን ይሰማ፣ መንግስትክፍተቱንተጨማሪሳንቲምበማተምለመሙላትቢሞክርእንኳንየተሰበሰበውን ሳንቲምመልሶወደገበያውበማስገባትየዋጋዝቅጠትመፍጠርየሚቻልበት ሁኔታ መኖሩንም በመግለጫው አትቷል። ድምጻችን ይሰማ የሚሰበሰበው ወይም ተቆጥቦ የሚቀመጠው ገንዘብ እጅ ላይ የገባው ሳንቲም በሙሉ አለመሆኑን ገልጿል።

ሳንቲምቆጥቦየመሰብሰብተቃውሞውየሚካሄደውበሁሉምየአገሪቱክልሎችእና ከተሞችሲሆን፣ ከፊታችንአርብ  ጀምሮማብቃቱእስኪገለጽድረስምላልተወሰነጊዜ ይቀጥላል ብሎአል።

ለወደፊቱአንድብርናከዛምበላይያሉየብር ኖቶችንምከመሰብሰብጀምሮሌሎችበአተገባበራቸውምሆነበእንድምታቸውጠንክረው እያደጉየሚሄዱየትብብርመንፈግእናየቦይኮትስልቶችንቀስበቀስበመለማመድሰላማዊ ትግሉን  እንደሚቀጥል ድምጻችን ይሰማ

አስታውቋል።

የሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ የኮሚቴ አባላት አሁንም ፈጣን ፍትህ ተነፍጎአቸው በእስር ላይ ይገኛሉ።