በጋዛ በሃማስ እንደታገተ የሚነገርለት ኢትዮ – እስራኤላዊ አድራሻው መጥፋት ዘረኝነት ነው ተባለ

ሐምሌ ፫ (ሶስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የ 26 ዓመቱ ወጣት መንግስቱ አቭራ ከመስከረም ወር ጀምሮ ያለበት አድራሻ አይታወቅም ፤ የእስራኤል መንግስትም ወጣቱን ለማፈላለግ ያደረገው ጥረት አለመኖሩ ዘረኝነት ነው ተብሎአል። በጋዛ በሃማስ እጅ እንደታገተ የሚነገረው ወጣት መንግስቱ፣ ቤተሰቦች “ልጃችን ያለበትን ሁኔታ ለማወቅ አልቻልንም ፣ መንግስትም ያለበትን ሁኔታ ለማወቅ የወሰደው ምንም ዓይነት እርምጃ አለመኖሩ ቅሬታ” ፈጥሮብናል ይላሉ። የጠቅላይ ሚንስቴር ...

Read More »

በጽናቷ የምትወደሰው ርእዮት አለሙ ተፈታች

ሐምሌ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ጸሀፊና መምህርት ርእዮት አለሙ በሽብር ወንጀል ተከሳ የ14 አመታት ጽኑ እስራት ከተፈረዳበት በሁዋላ፣ ለጠ/ፍርድ ቤት ይግባኝ በማለቷ የእስር ጊዜዋ ወደ 5 አመት ዝቅ እንዲል ተደርጎላታል። ያለፉትን ሶስት አመታት በአስቸጋሪ ሁኔታ በእስር ቤት ካሳለፈች በሁዋላ ፣ የኢህአዴግ መንግስት አመክሮ ጊዜዋ አልቋል በሚል ፈቷታል። ርዕዮት በብዙ ኢትዮጵያዊያን ዘንድ የጽናት ምልክት ተደርጋ ትወሰዳለች። ይህ ...

Read More »

ጠበቃ ተማም አባቡልጉ በፍትህ ሚኒስቴር የተጣለባቸው እገዳ ምንም አይነት ስነልቦናዊ ጫና እንደማይፈጥርባቸው ተናገሩ

ሐምሌ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፍትህ ሚኒስቴር በሽብረተኝነት ክስ ለሚከሰሱ ጋዜጠኞችና የሃይማኖት መሪዎችና የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችና አባላት ጠበቃ በመሆን የሚታወቁትን አቶ ተማም አባ ቡልጉን የዲሲፒሊን ግደፈት ፈጽመዋል በሚል ለአንድ አመት ከ7 ወር አግዷቸዋል። መታገዳቸውን ከሚዲያ የሰሙ ጓደኞቻቸው እንደነገሩዋቸው የገለጹት አቶ ተማም፣ በህጉ ቢሆን ነሮ የእግድ ደብዳቤው ከሚዲያ በፊት ለእርሳቸው መድረስ ይገባው እንደነበር ተናግረዋል። ድርጊቱ እርሳቸውን በህዝብ ...

Read More »

የምእራብ አርማጭሆ ወረዳ የሴቶች ሃላፊ ታሰረች

ሐምሌ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ምንጮች እንደገለጹት የኢህአዴግ አባል የሆነችው ወ/ሮ አስቴር ስዩም የወረዳው የሴቶች ጉዳይ ሃላፊ፣ በቅርቡ ደግሞ በጎንደር ከተማ የጥቃቅን እና አነስተኛ ድርጅት ሃላፊ በመሆን ስትሰራ ቆይታለች። አስቴር የኢህአዴግ አባል ብትሆንም ከበላይ አካል የሚመጣውን ትእዛዝ ሁሉ እንደወረደ የማትቀበል እንደሆነችና በዚህም የተነሳ የተለያዩ ማስጠንቀቂያዎች ተሰጥቷት እንደነበር፣ ከስራም ታግዳ መቆየቷን እርሷን በቅርብ የሚያዉቋት ይናገራሉ። የአንድ አመት ...

Read More »

ከባድ መሳሪያ የታጠቁ ከሶስት ሽህ በላይ የኢህአዴግ ወታደሮች አልሸባብን ለመውጋት በሚል ወደ ጌዶ ዘመቱ

ሐምሌ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ዘ ደይሊ ኔሽን የኢትዮጵያ ሰራዊት በታንክና በከባድ መሳሪያ ታግዞ በከተማዋ ውስጥ መታየቱን የአይን እማኞችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል። ሰራዊቱ የተንቀሳቀሰው ከኢትዮጵያ መሆኑንም የገለጸው ጋዜጣው፣አልሸባብ የሚቆጣጠረውን የባርደሬ ግዛት ለማስለቀቅ ሳያቅድ እንዳልቀረ ገልጿል። የአፍሪካ ህብረት ከኢትዮጵያ ያገኘውን ጨምሮ ከ20 ሺ በላይ ሰራዊት በሶማሊያ ቢያሰማራም አልሸባብን ለመደምሰስ አልቻለም። ታጣቂ ሃይሉ በቅርቡ በኢህአዴግ ሰራዊት ላይ በፈጸመው ...

Read More »

በኢነሳና በሃኪንግ ቲም መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ እንደነበር መረጃዎች አጋለጡ

ሐምሌ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ሃኪንግ ቲም ለተባለ ኩባንያ 1 ሚሊዮን ዶላር በመክፈል የስለላ መሳሪያዎችን የገዛው በአብዛኛው በህወሃት አባላት የሚመራው የደህንነት መስሪያ ቤት፣ ከኩባንያው ጋር ውዝግብ ውስጥ ገብቶ እንደነበርና ውዝግቡ ሳይፈታ መረጃው ይፋ መሆኑን ለህዝብ ይፋ ከሆነው መረጃ ለመረዳት ተችሎአል። ቢኒያም ተወልደ በተባለ የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ምሩቅ በኩል ግንኙነቱን የሚያደርገው የኢትዮጵያ የደህንነት መስሪያ ቤት ፣ የስለላ ሶፍት ...

Read More »

ከ24 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የጦር መሳሪያ ሊገዛ ነው

ሐምሌ ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የጦር ሃይሎች ኢታማዦር ሹም ጄ/ል ሳሞራ የኑስ ፣ ጠ/ሚኒስትሩን ጨምሮ ከፍተኛ የኢህአዴግ የጦር አዛዦች በተገኙበት የወታደራዊ ጥቅል አቋማቸውን አቅርበዋል። በከፍተኛ ሚስጢር በተካሄደው ስብሰባ ላይ ፣ ጄ/ል ሳሞራ ” ጦራችን ከጊዜው ጋር እየዘመነ አይደለም፣ የታንኮቻችን አቅም ያረጀ ነው፣ ተዋጊ አውሮፕላኖቻችን ከገበያ የወጡ ናቸው፣ መቀየሪያ እቃዎቻቸው ( ስፔር ፓርትስ) ከገበያ እየወጡና እየጠፉ ነው። ...

Read More »

በአዲስ አበባ ከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ እየተካሄደ ነው

ሐምሌ ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከትናንት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የተጠናከረ ጥበቃ እያደረጉ ሲሆን፣ በርካታ ወጣቶችና የመንግስት ሰራተኞችም እየታፈሱ መሆናቸውን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። በአዲስ አበባ የተቃዋሚ ሃይሎች ሰርገው ሳይገቡ ገብተዋል የሚል መረጃ ለደህንነት ክፍሉ እንደደረሰ የኢሳት ምንጮች ገልጸው፣ አሁኑ እንቅስቃሴም ከዚህ ጋር ሊያያዝ ይችላል ሲሉ ግምታቸውን አስፍረዋል። ለደህንነት ሲባል ኢሳት መረጃዎችን ...

Read More »

የሚኒስትር ሬድዋን አማካሪ መኮብለላቸው ተሰማ

ሐምሌ ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን አማካሪ የሆኑት አቶ አንዱዓለም አዱኛ አሞኘ ከሀገር መኮብለላቸውን ሰንደቅ ጋዜጣ ዘግቧል። አቶ አንዱዓለም በ2007 ምርጫ በኢሕአዴግ ጽ/ቤት ለቅስቀሳ የሚሆኑ ሰነዶችን እንዲያዘጋጁ ከመንግስት ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ተመድበው እንደነበር ጋዜጣው ዘግቧል። አቶ አንዱዓለም ከሀገር ከመኮብለላቸው በፊት ቀደም ብለው ባለቤታቸውንና ልጃቸውን ወደ አሜሪካ ማሻገራቸውን ጋዜጣው ዘግቦ፣ ግለሰቡ ከሚኒስትሩ ...

Read More »

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ መዝገብ በተከሰሱት ላይ ብይን ሳይሰጥ ቀረ

ሐምሌ ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሰማያዊ ፓርቲ፣ የአንድነት እና የዓረና ትግራይ አመራሮች የሺዋስ አሰፋ፣ አብርሃ ደስታ፣ ሀብታሙ አያሌው እና ዳንኤል ሺበሽን ጨምሮ 10 ተከሳሾች ሐምሌ 1/2007 ዓ.ም በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበው ፍርድ ቤቱ መዝገቡን መርምሮ ብይን ይሰጣል ተብሎ ቢጠበቅም፣ ብይኑን ሳይሰጥ ቀርቷል። ፍርድ ቤቱ የአቃቤ ህግ ምስክሮች ቃል በጽሑፍ ተገልብጦ ከመዝገቡ ...

Read More »