የዞን 9 ጦማሪያን “ዳኞች ስልጠና ላይ ናቸው” በሚል ምክንያት ፍርድ ቤት ለ38ኛ ጊዜ ተቀጠሩ

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በነሶልያ ሽመልስ የክስ መዝገብ በሽብረተኝነት በተከሰሱት ወጣት ጸሃፍት ላይ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ሲጠበቅ ዳኞች “አዳማ ስልጠና ላይ ናቸው” በሚል ለ38 ኛ ጊዜ እንዲራዘም ተደርጓል። ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት ለ5ኛ ጊዜ ቀጠሮ አራዝሟል። በአንድ መዝገብ ከተከሰሱት መካከል የተወሰኑት መለቀቃቸው፣ ቀሪዎቹም ይለቀቃሉ የሚል ተስፋ አሳድሮ ነበር። ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን ጸሃፊዎቹ እንዲፈቱ ጥያቄ ...

Read More »

አልሸባብ በደፈጣ ውጊያ ሁለት የኢትዮጵያ የጦር መኪኖችን ማውደሙን ገለፀ

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሶማሊያ ሰላም አስከባሪ ሰራዊት አሚሶል ስር ያለውን ንብረነታቸው የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት የሆኑትን ሁለት ወታደራዊ ተሽከርካሪዎችን በደቡባዊ ምዕራብ ሶማሊያ በጌዶ ግዛት በደፈጣ ውጊያ ማውደሙን አልሸባብ አስታውቋል። ጥቃቱ የተፈፀመው በአሊላን መንደር ውስጥ በአልሸባብና በኢትዮጵያ ሰራዊት መሃከል ለሰዓታት የቆየ የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ ነው። በአርፒጂ የጦር መሳሪያ ተሽከርካሪዎቹ መመታታቸውን የአካባቢው የዐይን እማኞች ተናግረዋል። በአልሸባብ ጥቃት ...

Read More »

በዲላ ከተማ መብራት በመጥፋት ነዋሪዎች ችግር ላይ መውደቃቸውን ተናገሩ

መስከረም ፳፯ (ኅያ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ላለፉት 4 ቀናት ያለማስጠንቀቂያ የተቋረጠው ኤሌክትሪክ፣ በንግድ ቤቶች እና በነዋሪዎች የእለት ተለት ህይወት ላይ ችግር ማስከተሉን ነዋሪዎች ገልጸዋል። የኤሌክትሪክ አገልግሎቱ የተቋረጠበት መንስኤ ለህዝቡ አለመገለጹንም ተናግረወዋል። ከዚህ በፊት በከተማው በተደጋጋሚ የ ኤሌክትሪክ መቋረጥ የሚከሰት ሲሆን ፣ ያሁኑ ደግሞ የተለየ ነው ሲሉ ነዋሪዎች በምሬት ይገልጻሉ። በከተማው በሳምንት አንድ ቀን ይቀርብ የነበረው የውሃ ስርጭትም ...

Read More »

በሳውድ አረቢያ በሃጅ ጸሎት ላይ በተፈጠረው አደጋ የሟቾች ቁጥር ጨመረ

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መስከረም 13 ቀን 2008 ዓም የሃጅ ጸሎት ለማድረስ ወደ አገሪቱ ከተጓዙት ኢትዮጵያውያን መካከል 47 ሙስሊሞች መሞታቸውን የእስልምና ጉዳዮች ጠ/ምክር ቤት አስታውቋል። 24 ጸሎት አድራሽዎች ቆስለው ከሆስፒታል ሲወጡ ፣ 2ቱ አሁንም ተኝተው በመታከም ላይ ናቸው። በእለቱ በደረሰው አደጋ የሳውዲ መንግስት 700 ሰዎች እንደሞቱ ቢናገረም፣ በእየለቱ የሚወጣው አሃዝ የሟቾች ቁጥር ከዚህም በላይ መሆኑን ...

Read More »

በእስር ላይ የሚገኙት የዞን 9 ጦማሪያን ካለምንም ቅድመ ሁኔታ በነፃ እንዲሰናበቱ ዓለምአቀፉ ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን ጠየቀ

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ቡድኑ ነገ ሃሙስ ክሳቸው ለ37ተኛ ጊዜ በፍርድ ቤት የሚታየውና በመፃፋቸው ብቻ በአሸባሪነት ክስ ተወንጅለው በእስር ላይ የሚገኙት አራቱ የዞን 9 ጦማሪያን ቡድን አባላት ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ክሳቸው ተቋርጦ በነፃ እንዲለቀቁ ሲል አሳስቧል። ካለፈው ዓመት ጀምሮ በእስር ላይ ከሚገኙት ጋዜጠኞች አጥናፍ ብርሃነ፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣አቤል ዋበላ እና ናትናኤል ፈለቀ እንደ አውሮፓዊያን ዘመን አቆጣጠር ...

Read More »

ጸረ ሙስና ወደ አንድ ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ከዝርፊያ ማዳኑን አስታወቀ

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ድርጅቱ በማካሄድ ላይ ባለው 11ኛ ጉባኤ በተለያዩ ክልሎች ከ937 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳኑን ገልጿል። ከክልሎች ሁሉ ከፍተኛ ገንዘብ ከስርቆት የዳነው በአማራ ክልል ነው ሲል አክሎ ጠቅሷል። በዚህ ጊዜ እንደተገለጸው ግልጽነት በጎደለው የግዢ ሂደት ሊባክን የነበረ ከ937 ሚሊየን ብር በላይ የህዝብ ገንዘብ ለማዳን ተችሏል። ከሙስና ጋር በተያያዘ ከ3 ሺ በላይ የመንግስት ሰራተኞች ...

Read More »

አስራ አራት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች በኬንያ ተያዙ

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በህገወጥ መንገድ ድንበር አቋርጠው ኬንያ ሲገቡ መንገድ ላይ ያዝኳቸው ያለውን አስራ አራት ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች የኬንያ ፖሊስ ይዞ ማቻኮስ ፍርድ ቤት አቅርቧቸዋል።ስደተኞቹ የቀረበባቸውን ክስ ያልተቀበሉት ሲሆን የሃያ ሽህ ሽልንግ የገንዘብ ቅጣት ወይም የመቶሰላሳ ቀናቶች የእስር ቅጣት እንደሚበየንባቸውና ቅጣቱን ከከፈሉ በኋላ ወደ አገራቸው እንደሚላኩም ተገልጿል። ስደተኞቹ በናይሮቢ ሞንባሳ አውራ ጎዳና በማቻኮስ በቹሙቪ የገበያ ...

Read More »

በጎንደር የፌደራል ፖሊስ አንድ የመዋለ ህጻናት ወስዶ አልመልስም አለ

መስከረም ፳፮ (ኅያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ነዋሪዎች እንደገለጹት በከተማው ቀበሌ 9 የድሃ ልጆች የሚማሩበትን መዋለ ህጻናት ትምህርት ቤት፣ ምርጫውን ሰበብ ተደርጎ ለፌደራል ፖሊስ በጊዜያዊነት ከተሰጠ በሁዋላ፣ ፖሊስ አለቅም በማለቱ ከነዋሪዎች ጋር ውዝግብ ተፈጥሯል። ፖሊስ በ15 ቀናት ቦታውን እንደሚለቅ ገልጾ፣ ትምህርት ቤቱን ቢረከብም፣ እስካሁን ድረስ ባለመልቀቁ ወላጆች ልጆቻቸውን ማስተማር አልቻሉም። ወላጆች አቤቱታ ለማቅርብ ብንሄድም በፖሊሶች ተደብድበናል በማለት ገልጸው፣ ...

Read More »

አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ አዲስ ካዋቀሩት ከቢኔ 5 የቀድሞ ሚኒስትሮችን ቀነሱ

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጠ/ሚኒስትሩ ካላካተቱዋቸው የቀድሞ ሚኒስትሮች መካከል የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ ሶፍያን አህመድ፣ የንግድ ሚኒስትሩ ከበደ ጫኔ፣ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ አለማየሁ ተገኑ፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትሩ አሚን አብዱልቃድር፣ የፕላን ኮምሽን ሚኒስትሩ አቶ መኮንን ማንያዘዋል ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም አቶ ሬድዋን ሁሴንን ከኮምኒኬሽን ሚኒስትርነት አንስተው የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ያደረጉዋቸው ሲሆን፣ የህዝበ ሙስሊሙን ጥያቄ በማወሳሰብ ሲወነጀሉ የነበሩት ዶ/ር ...

Read More »

በቴፒ ተጨማሪ ሰዎች ተገደሉ

መስከረም ፳፭ (ኅያ አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከአመት በላይ ለሆነ ጊዜ በውጥረት ውስጥ የምትገኘዋ የጋምቤላና የደቡብ አዋሳኝ ከተማ ቴፒ፣ ባለፈው አንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ ሶስት ዜጎች ተገድለውባታል። ከሳምንት በፊት የፌደራል ፖሊስ አባላት አንድ ሰው ከገደሉ በሁዋላ፣ ማንነታቸው በውል የማይታወቁ ሰዎች በወሰዱት የአጸፋ እርምጃ ደግሞ ከቴፒ 7 ኪሜትር እርቀት ላይ በምትገኝ ቀበሌ ውስጥ የሚኖሩ ሁለት የኢህአዴግ ካድሬዎችን ዛሬ ጠዋት ...

Read More »