.የኢሳት አማርኛ ዜና

የኢትዮጵያ መንግስት ከቻይና ባንክ ጋር የ500 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ፈረመ

መስከረም ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን በቻይ መንግስት ከተያዘው የቻይና የልማት ባንክ የ500 ሚሊዮን ዶላር ወይም የ8 ቢሊዮን ብር ብድር ማግኘቱ ታውቋል። ገንዘቡ የሚውለው ሁለት የስኳር ፋብሪካዎችን ለመገንባት መሆኑ ታውቋል። ለተመሳሳይ ፕሮጀክት መንግስት 394 ሚሊዮን ዶላር የሚሆን ብድር ከህንድ መንግስት ማግኘቱ ይታወሳል። ቻይና ለኢትዮጵያ መንግስት የሚሰጠው ብድር የወለድ መጠን አልታወቀም። ይሁን እንጅ ከቻይና የሚገኘው እርዳታ ...

Read More »

አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር የታዛዥነት እንጅ የአዛዥነት ስብእና የላቸውም ተባለ

መስከረም ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ኢትዮጵያን ለ 21 ዓመታት የገዙዋት አቶ መለስ ዜናዊ በህመም ምክንያት ከዚህ አለም በሞት ሲለዩ እርሳቸውን የተኩዋቸው አዲሱ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ፣  ትሁት፣ ቅንና ደግ ቢሆኑም፣ የህወሀት ባለስልጣናትን ተጋፍተው ለውጥ የሚያመጡ ሰው አለመሆናቸውን እርሳቸውን በቅርብ የሚያውቁና አብረዋቸው የሰሩ ሰው ለኢሳት ተናግረዋል። አቶ ሀይለማርያም ተሿሚዎቻቸውን እንደፈለጉ ለማሽከርከር ለሚፈልጉ የኢህአዴግ ባለስልጣናት የተመቸ ጠባይ ...

Read More »

ደቡብ ጎንደር እስቴ መካነ ኢየሱስ ውስጥ ህዝብ በጅምላ በፖሊስ እየተደበደበ መሆኑን በስፍራው የሚገኘው የኢሳት ወኪል ዘገበ

መስከረም ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የችግሩ መንስዔ በከተማዋ የሚያልፈው የመንገድ ፕሮጀክት በሌላ በኩል በማለፉ ምክንያት ህዝቡ በሰላማዊ ሰልፍ ተቃወሞውን ለማሰማት በመውጣቱ ነው። ለህዝቡ የታውሞ ሰልፍ የመንግስት ተወካዮች ምላሽ እንሰጣለን  ባሉት መሰረት የአካባቢው ነዋሪ  ቀና ምላሽ እየጠበቀ ባለበት ሁኔታ < ምላሽ እንሰጣለን >ያለው መንግስት ያሰማራው ልዩ ሃይል በትናንትናው ዕለት ሰልፈኛውን ህዝብ በጅምላ በቆመጥ ሲደበድብ ውሏል። የፖሊስ አባላቱ መውሰድ ...

Read More »

አቶ በረከት የኢቲቪና የፕሬስ ድርጅት ሥራ አስኪያጆችን አንስተው ታዛዦቻቸውን ሊሾሙ ነው ተባለ

መስከረም ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኮሙኒኬሽን ሚኒስትሩ አቶ በረከት ስምዖን  የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እና የኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ሥራ አስኪያጆችን በማንሳት ለእርሳቸው ታዛዥ የሆኑ ሰዎችን ለማስቀመጥ  እንቅስቃሴ መጀመራቸው ተጠቆመ። በዚህም መሰረት ከደቡብ ክልል ያስመጡትና በኢትዮጵያ ራዲዮ ውስጥ በምክትል ሥራ አስኪያጅነት ሢሰራ የቆየው ሰለሞን ተስፋዬ የኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣የ አዲስ ዘመን ጋዜጣ ምክትል ዋና ...

Read More »

የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ የነበሩት ኮበለሉ

መስከረም ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በአሁኑ ወቅት በኃላፊነት ላይ ባለው የኩማ አስተዳደር የአዲስአበባ ከተማ ምክትል ከንቲባና የማስታወቂያ ቢሮ ኃላፊ በመሆን ያገለገሉትና ከአንድ ዓመት በፊት በአቅም ማነስ ተተችተው ከኃላፊነታቸው የተነሱት አቶ ከፍያለው አዘዘ ወደ ዩናይትድስቴትስ አሜሪካ ቤተሰባቸውን ይዘው መኮብለላቸው ተሰማ፡፡ አቶ ከፍያለው ከ1997 ዓ.ም ምርጫ አለመግባባት ጋር በተያያዘ በገዥው ፓርቲ ተሹሞ የነበረውን የባለአደራውን የአቶ ብርሃነ ደሬሳ አስተዳደር በግንቦት ...

Read More »

የአሜሪካ መንግስት የአቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ሹመት ታሪካዊ ነው አለ

መስከረም ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የፕሬዚዳንት ኦባማ አስተዳደር በኢትዮጵያ የታየው የስልጣን ሽግግር ታሪካዊ፣ ሰላማዊና ህገመንግስታ ነው በማለት አወድሶታል። አሜሪካ ከአቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ጋር ጥሩ የሆነ ግንኙነት መመሰርቷን የገለጠው መግለጫ ፣ በሚቀጥሉት አመታት የኢኮኖሚ ግንኙነቱን ለማጠንከር፣ ሰብአዊ መብቶችንና ዲሞክራሲን ለማጎልበት እንዲሁም የአካባቢውን ጸጥታ ለማስጠበቅ ከእርሳቸው ጋር በጋራ እንደሚሰራ አስተዳደሩ ገልጧል። የአሜሪካ መንግስት አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ...

Read More »

ሲሉ አቶ ስብሀት ነጋ ተናገሩ

መስከረም ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የህወሀት መስራች የሆኑት አቶ ስብሀት ነጋ ይህን ያሉት ሰሞኑን ለንባብ ከበቃው አዲስ ጉዳይ መጽሔት ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ ነው። ቀደም ሲል  የህዝባዊ ወያነ ሀርነት ትግራይ-ህወሀት ሊቀ-መንበር ሆነው የተመረጡት አቶ አባይ ወልዱ ብሔራዊ እርቅ  የሚለው ጥያቄ  ፈጽሞ ተቀባይነት እንደማይኖረውና  ጥያቄውን የሚያነሱ ሀይሎችን  እንደሚታገሏቸው  መናገራቸው ያታወሳል። የአቶ አባይ ወልዱ  አባባልም ሆነ፤ አቶ ስብሀት ለ አዲስ ...

Read More »

በኮሪያ የኢትዮጵያ ኢምባሲ የባጀት ጥረት ገጠመው

መስከረም ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በደቡብ ኮሪያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ በበጀት ዕጥረት ምክንያት እኤአ 2001  በሩን ዘግቶ ከተመለሰ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ በ2012  ቢከፈትም ገና ስራውን ከጀመረ 3 ወራትን ሳያስቆጥር ዳግመኛ የበጀት እጥረት እንደገጠመውና ለሰራተኞቹ የሚከፍለው ደመወዝ እንዳጣ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ የውስጥ ሰራተኛ አስታወቁ።   ሰራተኛው ለኢሳት በላኩት መልእክት ኢምባሲው በከፍተኛ የገንዘብ ቀውስ ውስጥ ይገኛል።   ለሰራተኞቹ ሊጠበቁ ...

Read More »

በተባበሩት ዓረብ ኢምሬት በሻርጃህ ከተማ 36 ኢትዮጵያውያን ሴቶች ታሰሩ

መስከረም ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ኢምሬት ኒውስ እንደዘገበው ኢትዮጵያውያኑ በሻርጃህ ፖሊስ የታሠሩት ከስፖንሰሮቻቸው ጠፍተው በመገኘታቸው ነው። ኢትዮጵያውያኑ  በኢምሬት -አረብ ቪላ ውስጥ እንደሚገኙ መረጃ ከደረሰው በሁዋላ በቁጥጥር ሥር  እንዳዋላቸው የገለጸው የሻርጃህ ፖሊስ፤ በህገ-ወጥ መንገድ በሥራ ተሰማርተው እንደነበር አመልክቷል። ጉዳያቸው ወደ አቃቤ ህግ ተልኮ በሁሉም ላይ ክስ እንደሚመሰረትባቸውም ፖሊስ አስታውቋል። በተመሣሳይ መንገድ የተሰማሩ ስደተኞች ካሉ ህዝቡ መረጃ እንዲሰጥ የሻርጃህ ...

Read More »

የኬንያ የአፍሪካ ህብረት ጦር የሶማሊያ ሲቪሎችን ገደለ

መስከረም ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በሶማሊያ ከአልሸባብ ተዋጊ ሀይል ጋር በመፋለም ላይ የሚገኘው የኬንያ ሰራዊት ፣ የአልሸባብ ዋና መናገሻ ወደ ሆነችው ኪስማዮ ከተማ ሲያመራ ፣ ሰባት ንጹሀን ዜጎችን መግደሉን ቢቢሲ ዘግቧል። የሶማሊያ መንግስት ጦር ቃል አቀባይ የሆኑት አዳን ሙሀመድ ሂርሲ ግድያው ሆን ተብሎ የተፈጸመ መሆኑን አጋልጠዋል። እንዲህ አይነቱ ድርጊት ስሜትን የሚጎዳ ነው በማለት በአንድ ሱቁ ፊት ለፊት ...

Read More »