ሰኔ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በባሌ ሮቤ እና በጎባ ከተማ በቅርቡ ኢሳትን ሲመለከቱ የተገኙ ሰዎች ገናሌ እየተባለ በሚጠራው እስር ቤት ውስጥ መታሰራቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ግለሰቦቹ የተያዙት በተለያዩ ሰበቦች ቢሆንም ፍርድ ቤት ሲቀርቡ የሚቀርብባቸው ክስ ግን የተቃዋሚ ጣቢያ የሆነውን ኢሳትን ሲመለከቱ ተገኝተዋል የሚል ነው። ከታሰሩት መካከል ወጣቶች እና አረጋውያን እንደሚገኙበት የደረሰን መረጃ ያመለክታል። የፕሬስ ነጻነት ተከብሮአል በሚባልባት ኢትዮጵያ ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
የአሜሪካ ኮንግረስ በኢትዮጵያ የዲሞክራሲ ግንባታ ዙሪያ አስተያየቶችን ሊሰማ ነው
ሰኔ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የአሜሪካ ኮንግረስ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ከታዋቂ የውጭ አገር ዜጎች እና ኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ አስተያየቶችን እኤአ ሰኔ 20 ይሰማል። ከኢትዮጵያ የግንቦት7 ሊቀመንበር እና በበክኔል ዩኒቨርስቲ የኢኮኖሚክስ ተባባሪ ፕሮፌሰር የሆኑት ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ እና የሶሊዳሪቲ ሙቭመንት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ኦባንግ ሜቶ አስተያየታቸውን የሚሰጡ ሲሆን፣ ከውጭ አገር ሰዎች መካከል ደግሞ በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ...
Read More »አንድነት ፓርቲ ግብጽና ኢትዮጵያ ከጸብ አጫሪነት ድርጊት እንዲቆጠቡ ጠየቀ
ሰኔ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ፓርቲው ” ሁሉንም ነገር ለፖለቲካ ፍጆታ ለማዋል የቆረጠ ፓርቲ የሀገርን ሉዓላዊነት አደጋ ላይ መጣሉ የማይቀር ነው” በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ ” የግብጽና የኢትዮጵያ መንግሥት ከፀብ አጫሪ ድርጊት እንዲቆጠቡ፣ የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን ከሚያበላሹ ፕሮፓጋንዳዎችን ከመንዛት እንዲታቀቡና ለዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጠረጴዛ ዙሪያ ንግግሮች ላይ እንዲያተኩሩ አሳስቦአል።” አባይን መጠቀም የኢትዮጵያ ተፈጥሮዊ መብት መሆኑ እንዲታወቅ፣ሁለቱ ሀገሮች የአባይን ጉዳይ ...
Read More »ከ 30 በላይ አረጋውያን ያለምንም ጥያቄ ታስረው ይገኛሉ ሲሉ ቤተሰቦቻቸው አስታወቁ
ሰኔ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በኦሮምያ ክልል በጎሬ ወረዳ በንግድ ስራ ይተዳደሩ የነበሩ ከ30 በላይ አረጋውያን ካለፉት 8 ወራት ጀምሮ በእስር ላይ እንደሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ለኢሳት ገልጸው፣ የወረዳው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር እውነቱ በቀለ አረጋውያኑ መታሰራቸውን አምነዋል። አብዛኞቹ እስረኞች እድሜያቸው በ65 እስከ 80 መካከል ሲሆን፣ ብዙዎች እስሩን መቋቋም አቅቷቸው ለተለያዩ በሽታዎችና የመንፈስ ጭንቀት ተዳርገዋል። አረጋውያኑ በ2001 ዓም የከተማውን መንገድ ለመስራት ...
Read More »የተምች ወረርሺኝ በመላ ሃገሪቱ ቡቃያዎችን እያጠቃ ነው፡፡
ሰኔ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የፀረ ሰብል ተባይ ወይም ተምች ወረርሽኝ በአማራ በኦሮሚያ ዞን፣ በምስራቅ ጎጃም፣ በደቡብ ጎንደር፣በሰሜንና በደቡብ ወሎ፣ በትግራይ ደቡባዊ ዞን በአላማጣና ራያ አዘቦ ወረዳዎች ቡቃያዎችን እያጠፋ ነው፡፡ በባህላዊ ዘዴዎችና በኬሚካል ርጭት ለመከላከል ሙከራ ቢደረግም ለውጥ አለመምጣቱን የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ የተምች ተባይ ወረርሽኝ በአማራ በምስራቅ ጎጃም በ11 ወረዳዎች ውስጥ በ12 ሺ 849 ሄ/ር የሰብል ማሣ ላይና ...
Read More »ፍርድ ቤት የባንክ ሂሳባቸውን ያገደባቸው የመንግስት ባለስልጣናትና ባለሀብቶች ዝርዝር ይፋ ሆነ
ሰኔ ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የፌዴራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት በቁጥር የኮ/መ/ቁ 134048 ግንቦት 13 ቀን 2005 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ 429 የመንግሥት ኃላፊዎችና ባለሃብቶች በመንግሥትና በግል ባንኮች ያላቸው ገንዘብ የታገደባቸው መሆኑን ፣ የአንዳንዶች ደግሞ የድርጅታቸው የባንክ ሂሳብና መኪኖቻቸው እንዲታገድባቸው ትእዛዝ አስተላልፎአል። ይፋ የሆነው ዝርዝር እንደሚያሳየው ከሙስና ጋር በተያያዘ የተከሰሱት ሰዎች ቤተሰቦች እና ዘመዶች የባንክ ሂሳብ ቁጥር እንዲታገድ ተደርጓል። ከባለሀብቱ ...
Read More »በደቡብ ጎንደር ዞን መምህራን በደህንነት ሀይሎች ታፍነው ተወሰዱ
ሰኔ ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በደብረ ታቦር ከተማ ከአማራ ዲሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ እና ከግንቦት 7 ጋር ግንኙነት አላችሁ የተባሉ መምህራን ትናንት ማታ እና ዛሬ ጠዋት በደህንነት ሐይሎች ታፍሰው ወዳልታወቀ ቦታ መወሰዳቸውን ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። መምህር ታደሰ መንግስቴና መምህር ፈቃዱ ጌትነት የሚባሉ በ ፈቀደ እግዚ ኮሌጅ ውስጥ አስተማሪዎች ሲሆኑ መምህር አሸናፊ አለሙ ደግሞ የሁለተኛ ደረጃ ...
Read More »የደሴ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ከስራ ተባረሩ
ሰኔ ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የአማራ ክልል የአሰተዳደር እና ጸጥታ ዘርፍ ቢሮ በተለያዩ ዞኖች በሚገኙ የጸጥታ ሀይሎች ላይ ግምገማ ሲያደርግ መቆየቱን ተከትሎ የደሴ ከተማ ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ደረጀ እንዲባረሩ ተደርጓል። በቅርቡ ኢሳት ይፋ ባደረገው የድምጽ ማስረጃ፣ የከተማዋ ነዋሪዎች ፖሊስ ከፍተኛ የሰብአዊ መብቶችን እየጣሰ መሆኑን፣ የቀንና የሌሊት ዘረፋ ተባብሶ መቀጠሉን እንዲሁም በእስልምና እምነት ተከታዮች ላይ ኢሰብአዊ ድርጊቶች መፈጸማቸውን ...
Read More »የፊታችን እሁድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከደቡብ አፍሪካው ብሔራዊ ቡድን ጋር በአዲስአበባ ስታዲየም የሚያካሂደው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ወሳኝ ግጥሚያን በመሃል ዳኝነት የሚመሩት ግብጻዊ ዳኛ በመሆናቸው ጨዋታው በሰላም የመጠናቀቁ ጉዳይ ላይ ከፍተኛ ስጋት አሳድሯል
ሰኔ ፮ (ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የፊታችን እሁድ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከደቡብ አፍሪካው ብሔራዊ ቡድን ጋር በአዲስአበባ ስታዲየም የሚያካሂደው የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ወሳኝ ግጥሚያን በመሃል ዳኝነት የሚመሩት ግብጻዊ ዳኛ በመሆናቸው ጨዋታው በሰላም የመጠናቀቁ ጉዳይ ላይ ከፍተኛ ስጋት አሳድሯል። ኢትዮጵያ እያስገነባችው ያለችው የአባይ ግድብ አቅጣጫውን እንዲቀይር መደረጉን ተከትሎ በግብጽ ከተቀሰቀሰው ሕዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ ግብጻዊው ዳኛ በአዲስአበባ ስታዲየም ዛቻ፣ ስድብና ...
Read More »ወደሶማሌ ክልል ተጉዞ የነበረው የአርቲስቶችና የጋዜጠኞች ቡድን በክልሉ አስተማማኝ ሰላም እንዳለ ምስክርነቱን በመስጠት የአንድ ሳምንት ጉዞውን ሰኞ ዕለት አጠናቀቀ
ሰኔ ፭ (አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ቡድኑ ከጎዴ ተነስቶ በቀብሪደህር፣ በደገሃቡር፣ በቀብሪበይህ፣ በጂጂጋ አድርጎ ወደሐረር በመግባት የሳምንት ጉዞውን በድሬዳዋ ከተማ ባለፈው እሁድ አጠናቋል፡፡ በጉዞው ወቅት በአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ከፍተኛ ጥበቃ እየተደረገለት የተጓዘው የዚሁ ቡድን አባላት ከሆኑት መካከል፤ አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ፣ደበሽ ተመስገን፣ጥላሁን ጉግሳ፣ችሮታው ከልካይ፣አብራር አብዶ፣ አበበ ባልቻና የመሳሰሉ አርቲስቶችና ጸሐፊዎች “በሶማሌ ክልል ፍጹምና አስተማማኝ ሰላም አለ” በሚል ምስክርነት የሰጡ ...
Read More »