.የኢሳት አማርኛ ዜና

የሕወሃት ማዕከላዊ ኮሚቴ ርምጃ የወሰደው በክልሉ አመራሮች ላይ ብቻ ነው ታባለ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 20/201)የሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ/ሕወሃት/ማዕከላዊ ኮሚቴ በመቀሌ ሲያካሂድ በቆየው ስብሰባ ከፍተኛ ግምገማ ያደረገውና ርምጃ የወሰደው በዋናነት በትግራይ ክልል በሃላፊነት ላይ በሚገኙ አመራሮች ላይ መሆኑን ለስርአቱ ቅርበት ያላቸው የተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ። አቶ አባይ ወልዱ ከፓርቲው ሊቀመንበርነትና ስራ አስፈጻሚነት የተነሱት የትግራይና የአማራ ክልልን ወሰን ውዝግብ በቶሎ ባለመቅጨት ትግሬዎችን ለጥቃት አጋልጠሃል በሚል እንደሆነም ተመልክቷል። ከወሰን ውዝግቡ ጋር በተያያዘ የተነሳውን ግጭት ተከትሎ ...

Read More »

በቦረና የመከላከያ ሰራዊት አባላት ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ፈጽመዋል ተባለ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 19/2010) የመከላከያ ሰራዊት አባላት በወገን ቀርቶ በጠላት ላይ የማይደረግ ኢ ሰብአዊ ድርጊት ፈጽመዋል ሲል የቦረና አስተዳደር ቅሬታውን አቀረበ። ድርጊቱን የፈጸሙ የመከላከያ አባላት ተላልፈው እንዲሰጡና ለህግ እንዲቀርቡም ጠይቋል። በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት የቦረና ዞን አስተዳደር ጽሕፈት ቤት በሕዳር 14/2010 ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት፣ለመከላከያ ሚኒስቴርና ለኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት በጻፈው ደብዳቤ የመከላከያ ሰራዊት ያደረሰውን ኢ-ሰብአዊ ድርጊት በዝርዝር አስፍሯል። ደብዳቤው በቦረና ዞን ድሬ ...

Read More »

የሕወሃትን አገዛዝ የሚያወግዙ ሕዝባዊ ተቃውሞዎች እንደቀጠሉ ነው

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 19/2010) የሕወሃትን አገዛዝ የሚያወግዙ ሕዝባዊ ተቃውሞዎች ተጠናክረው መቀጠላቸው ተነገረ። የሃሮማያና የጅማ ዩኒቨርስቲ ተመሪዎች በተቃውሞ ላይ ናቸው። 35ሺ የሃሮማያ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ግቢያቸውን ለቀው ሲወጡ የጅማዎቹ ደግሞ ከግቢያቸው እንዳይወጡ ታግተዋል። በጋሞጎፋ ዞን ሳውላ፣አወዳይ እንዲሁም በወለጋ ሕዝባዊ ተቃውሞው እንደገና ተቀጣጥሏል። በኢትዮጵያ የሕወሃትን የ26 አመታት አገዛዝ ለማክተም በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚካሄደው ተቃውሞ እንደቀጠለ ይገኛል። በጋሞጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በግብር የተንገሸገሸው ነዋሪ የገቢዎችና ...

Read More »

የኬንያ ፕሬዝዳንት ቃለ መሃላ ፈጸሙ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 19/2010) የኬንያ ፕሬዝዳንት ሆነው የተመረጡት ኡሁሩ ኬንያታ ዛሬ ቃለ መሃላ ፈጸሙ። ተቃዋሚው ራይላ ኦዲንጋ ግን ኬንያታ የተመረጡት ዝቅተኛ ቁጥር ባላቸው ድምጽ ሰጪዎች በመሆኑ በሚቀጥለው ወር ራሳቸው የፕሬዝዳንትነት ቃለመሃላ እንደሚፈጽሙ ለደጋፊዎቻቸው ተናግረዋል። ከሁለት አጨቃጫቂ ምርጫዎች በኋላ የኬንያ ፕሬዝዳንትነትን መንበር ለሁለተኛ ጊዜ የተቆጣጠሩት ኡሁሩ ኬንያታ ቃለ መሃላቸውን ሲፈጽሙ ተቃዋሚዎች በስነስርአቱ ላይ አለመታደማቸው ታውቋል። ኬንያታ በንግግራቸው ሁሉን አቀፍ ስሜት ለመፍጠር በተቃዋሚዎች ...

Read More »

የኢሳት 7ኛ አመት በኮሎምቦስ ኦሃዩ ተከበረ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 19/2010)የኢሳት 7ኛ አመት በኮሎምቦስ ኦሃዩ በድምቀት ተከበረ። በበአሉ ላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግልና የኢሳት ድርሻ በሚል ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል። ቅዳሜ ህዳር 25/2017 በኦሃዩ በተከበረው የኢሳት 7ኛ አመት ላይ ከኦሃዩና አካባቢዋ፣ከሴንሴናቲ፣ከዴይተን፣ክሊቭላንድና ኢንዲያና ግዛት የመጡ የኢሳት ደጋፊዎች ተሳትፈዋል። በዝግጅቱ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት ኮመዲያን ክበበው ገዳና የኢሳት ባልደረባው አቶ ኤርሚያስ ለገሰ ሲሆኑ ኮመዲያን ክበበው ገዳ ለዝግጅቱ ልዩ ድምቀት ሰጥቶት ነበር። ...

Read More »

ሰላም ባስ ገራዥ ላይ ጥቃት ፈጽመዋል ተብለው በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ ክስ ተመሰረተ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር19/2010)በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው የሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ/ሕወሃት/ንብረት በሆነው ሰላም ባስ ገራዥ ላት ጥቃት በመፈጸም የተጠረጠሩ ግለሰቦች ክስ ተመሰረተባቸው። አቃቢ ህግ ግለሰቦቹ ድርጊቱን የፈጸሙት በአርበኞች ግንቦት ሰባት ትዕዛዝ ነው ሲልም አመልክቷል። አርብ ሕዳር 15/2010 በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች አንተነህ ፋንታሁን፣ኤርሚያስ አለባቸው፣አንድነት ፋንታሁን፣ፍስሃ እያዩና ብርሃኑ ሞገስ የተባሉ መሆናቸውም በክሱ ተመልክቷል። እኒዚህ በክሱ ላይ የተዘረዘሩት ...

Read More »

የሮበርት ሙጋቤ የልደት ቀን ብሔራዊ የወጣቶች ቀን ሆኖ እንዲከበር ታወጀ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 18/2010) በዚምባቡዌ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሮበርት ሙጋቤ የልደት ቀን ብሔራዊ የወጣቶች ቀን ሆኖ እንዲከበር ታወጀ። ባለፈው ሳምንት ስልጣኑን የተረከቡት ኤመርሰን ናንጋግዋ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ከዚምባቡዌ መስራች መሪዎች አንዱ በመሆናቸው ክብር ይገባቸዋል ብለዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ሮበርት ሙጋቤ ከስልጣን እንዲወርዱ በተደረገ ድርድር 10 ሚሊየን ዶላር የጡረታ ጉርሻ እንደተፈቀደላቸው ዘገባዎች ያሳያሉ። ባለፈው ሳምንት በጦር ሃይሉና በአስታራቂዎች ግፊትና ድርድር የስልጣን መልቀቂያቸውን አስገብተው ወደ ...

Read More »

የዮናታን ተስፋዬ ክስ ከሽብርተኝነት ክስ ወደ መደበኛ ወንጀል ተቀየረ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 18/2010)የቀድሞ የሰማያዊ ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የነበረው ዮናታን ተስፋዬ ተከሶበት የነበረው የሽብር ተግባር ክስ ተሰረዘለት። ክሱ ወደ መደበኛ ወንጀል የተቀየረው የፍርድ ሂደት የዮናታን የእስር ቤት ቆይታንም ከ6 አመት ወደ 3 አመት ዝቅ እንዲል አድርጎታል። ይህ በእንዲህ እንዳለም የወልቃይት አማራ ማንነት ኮሚቴ አባላት ዳኛ ዘርአይ ወልደሰንበት ከችሎት እንዲነሱላቸው ለፍርድ ቤት ያቀረቡትን አቤቱታ በፅሁፍ ማስገባታቸው ታውቋል። በታህሳስ 2008 ነበር በኦሮሚያ ...

Read More »

በቱርክ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አታሼ በኢትዮጵያና በቱርክ መሃል ጦርነት እጭራለሁ አሉ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 18/2010)በቱርክ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አታሼ ተስፋኪሮስ ሃይሉ ገብረማርያም በኢትዮጵያና በቱርክ መሃል ጦርነት እጭራለሁ ሲሉ ማስፈራራታቸው ተገለጸ። አታሼው ይህን ያሉት በስካር መኪና ሲያሽከረክሩ አደጋ ማድረሳቸውን ተከትሎ በፖሊስ በመጠየቃቸው ነው። በቱርክ አንካራ ቅዳሜ ለሌት አደጋውን ያደርሱት አቶ ተስፋኪሮስ ሁለት ተሽከርካሪዎችን የገጩ ሲሆን አንድ ሰው ማቁሰላቸውም ታውቋል። በሎሳንጀለስ የኢትዮጵያ ቆንስላ ተጠባባቂ ዳይሬክተር ጄነራል ሆነው ሰርተዋል። በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥ በተለያዩ ሃላፊነቶች ቆይተዋል። ...

Read More »

በታላቁ ሩጫ ኮከብ የሌለበት ባንዲራ በፖሊስ ሲቀማ ዋለ

(ኢሳት ዜና–ሕዳር 18/2010)በታላቁ ሩጫ ውድድር ኮከብ የሌለበትን ባንዲራ የያዙ ኢትዮጵያውያን በፖሊስ ሲነጠቁ መዋላቸውን በስፍራው የነበሩ ምንጮች ለኢሳት ገለጹ። የቴዲ አፍሮን ምስልና “ኢትዮጵያ” የተሰኘውን የዜማውን አርማ የያዘ ካኒቴራ የለበሱ ወጣቶችም ከታላቁ ሩጫ ውድድር እንዲወጡ ተደርገዋል። የሼህ መሀመድ አላሙዲ አድናቂዎች “አይዞህ አባቴ”የሚልና የእሳቸውን ፎቶ ለጥፈው ሲሮጡ ግን ከውድድሩ እንዲታገዱ አልተደረጉም። በታላቁ ሩጫ ላይ 44ሺህ ተሳታፊዎች ለውድድሩ ድምቀት ሰጥተውት ነበር። በዚህ ውድድር ላይም ...

Read More »