.የኢሳት አማርኛ ዜና

ሁለት የስውዲን ፓርላማ አባላት ለመንግስታቸው ጥሪ አቀረቡ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 30/2010) ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸመ ያለውን ግድያና የሰብአዊ መብት ጥሰት ችላ ከማንልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል ሲሉ ሁለት የስውዲን ፓርላማ አባላት ለመንግስታቸው ጥሪ አቀረቡ። አንድሬስ አስተርበርግና ማሪያ አንደርሰን የተባሉ የስዊዲን ፓርላማ አባላት በኢትዮጵያ የሚፈጸመውን ጭፍጨፋ በቸልታ የምናየው ከሆነ አጠቃላይ የእርስ በርስ ጦርነት ሊከሰት ይችላል ሲሉ አስተጠንቅቀዋል። የስውዲን መንግስትም አስቸኳይ ምላሽ እንዲሰጥ በሚል ጥያቄ ያቀረቡት አባላቱ ከዚህ በኋላ ከኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ ...

Read More »

በአማራ ክልል ከ20 በላይ ሰዎች ተገድለዋል ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 30/2010) በአማራ ክልል ተደጋጋሚና ድንገተኛ ጥቃት ባለፈው ወር ብቻ በአገዛዙና በመንግስት ተቋማት የስራ ሃላፊዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት ከ20 በላይ ሰዎች መሞታቸውን በብሔራዊ የጸጥታና ደህንነት ምክር ቤት ላይ የቀረበ ሪፖርት አመለከተ። ከሟቾቹ መካከል የቀበሌና የወረዳ አስተዳደር ባልደረቦች እንደሚገኙበት ከአማራ ክልል ለምክር ቤቱ የቀረበው ሪፖርት ያስረዳል። የብሔራዊ፣ የጸጥታና ደህንነት ምክር ቤት ከዚህ በፊት የወጣውን እቅድ እንደገና በመከለስ አዲስ የጋራ ዘመቻ ...

Read More »

በቄሮዎች ላይ ምርመራ ተጀመረ ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 30/2010) የኦሮሞ ወጣቶች እያደረጉ ያሉት ትግል ያሳሰበው የሕወሃት አገዛዝ በቄሮዎች ላይ ምርመራ ጀመርኩ አለ። የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ኦፌኮ ምርመራውን ከንቱ ድካም ሲል አጣጥሎታል። የፌደራል ፖሊስ ቄሮ ተብሎ በሚጠራው ቡድን ላይ ምርመራ ጀመርኩ ባለበት መግለጫ በአንዳንድ የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች የመንግስት መዋቅር ሙሉ በሙሉ መፍረሱን ያመነበት መሆኑ ታውቋል። የአቶ ለማ መገርሳ ቡድን ከእጃችን አልወጣም የሚል መልዕክት ለማስተላለፍ የታሰበ መግለጫ ነው ...

Read More »

ለኦሮሞና ለአማራ ተወላጆች የጄኔራልነት ማዕረግ ሊሰጥ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 30/2010) የመከላከያ ሰራዊቱን በተመለከተ የሚነሱ ተቃውሞዎችን ተከትሎ ለኦሮሞና ለአማራ ተወላጆች የጄኔራልነት ማዕረግ ለመስጠት መወሰኑን ምንጮች ለኢሳት ገለጹ። ማዕረጉ ይሰጣቸዋል የተባሉት መኮንኖች ለተሃድሶ ስልጠና መግባታቸው ተመልክቷል። የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት በመከላከያ ሰራዊቱ አመራር ውስጥ ያለውን ውጥረት በመቃወም የሚደረጉ ግፊቶችን ተከትሎ የአመራር ቦታዎቹን ከማስተካከል ይልቅ አዳዲስ ግለሰቦችን ከሌላ ብሔረሰብ ለመሾም ዝግጅት መጠናቀቁን መረዳት ተችሏል። ከ30 የማያንሱ ሰዎች ይሾሙበታል በተባለው በዚህ ፕሮግራም ...

Read More »

ኡጋንዳ እጩዎች ላይ የጣለችውን የዕድሜ ገደብ አነሳች

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 27/2010) ኡጋንዳ ለፕሬዝዳንትነት በሚወዳደሩ እጩዎች ላይ የጣለችውን የዕድሜ ገደብ አነሳች። ርምጃው ፕሬዝዳንት ዮዎሬ ሞሶቬኒ እድሜያቸው ለተጨማሪ ፕሬዝዳንታዊ ውድድር አለመፍቀዱን ተከትሎ የተነሳ እንደሆነም ታውቋል። የኡጋንዳ ፓርላማ በኡጋንዳ ሕገመንግስት ላይ የተቀመጠውን የዕድሜ ጣሪያ ያነሳው 317 ለ97 በሆነ የድምጽ ብልጫ እንደሆነም አልጀዚራ በዘገባው ላይ አስፍሯል። እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ1995 የታወጀው የኡጋንዳ ሕገመንግስት ዕድሜው 35 አመት ያልደረሰና ከ75 አመት ያለፈው የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ...

Read More »

ወጣቱ በፍርድ ቤት ጉዳቱን እንዳያሳይ ተከለከ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 14/2010) በማዕከላዊ የማሰቃያ እስር ቤት ከፍተኛ ስቃይ የደረሰበት ወጣት በፍርድ ቤት ጉዳቱን እንዳያሳይ ተከለከ። ወጣት ፈዲሳ ጉታ በማዕከላዊ እስር ቤት ከፍተኛ ሰቆቃ የተፈጸመበት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ማዕከላዊን በተመለከተ አነጋጋሪ የሆነ መግለጫ በሰጡበት በዚሁ ሳሞን ነው። ዳኞች ፈዲሳን ጉዳቱን እንዳያሳይ ከከለከሉት በኋላ የደበደቡህን ክሰሳቸው ማለታቸው ተገልጿል። ወጣት ፈዲሳ ጉታ የታሰረው ከወለጋ ነው።የተከሰሰው በኦነግ ስም ሲሆን የሽብር ተግባር ለመፈጸም በማቀድና ...

Read More »

ከ14ሺ በላይ ሕጻናት ከቤተሰቦቻቸው ጋር መለያየታቸው ታወቀ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 27/2010)   በኦሮሚያና ሶማሌ ክልል በተፈጠረው ግጭት ከ14ሺ በላይ ሕጻናት ከቤተሰቦቻቸው መለያየታቸውን ዩኒሴፍ አስታወቀ። በሁለቱ ክልሎች በተፈጠረ ግጭት ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉት ደግሞ ከ84 ሺ በላይ ሕጻናት መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት የሕጻናት መርጃ ድርጅት ይፋ አድርጓል። በኦሮሚያና ሶማሌ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ያለው ግጭት ካለፈው ታህሳስ ወዲህ ለመገመት የሚያስቸግር ቀውስ መፍጠሩን የዩኒሴፍ ሪፖርት ያመለክታል። እንደ ዩኒሴፍ ገለጻ በግጭቱ በተለይ ሕጻናትና እናቶች ...

Read More »

በወለጋ ሻምቡ አፈሳ እየተካሄደ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 27/2010) በወለጋ ሻምቡ በቅርቡ ከተካሄደው ሕዝባዊ ተቃውሞ ጋር በተያያዘ አፈሳ እየተካሄደ መሆኑን የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አስታወቀ። ከትላንት ምሽት ጀምሮ በርካታ የሻምቡ ነዋሪዎች ታፍሰው ተወስደዋል። በተያያዘ ዜና በምዕራብ ሸዋ ሻሸመኔ አካባቢም ግጭት መፈጠሩ ታውቋል። በሀረሪ ክልል ኤረር ወረዳ የፌደራል ፖሊስ አንድ አርሶአደር መግደሉን ተከትሎ ውጥረት መንገሱን ከአካባቢው ያገኘነው መረጃ አመልክቷል። ባለፈው እሁድ በሻምቡ የተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ለኢሕአዴግ የቅዳሜው መግለጫ ...

Read More »

እየተወሰደ ያለው ርምጃ በውጭ ግንኙነቱ ላይ ትልቅ ፋይዳ አለው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 27/2010) የኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እየወሰደ ያለው ርምጃ በውጭ ግንኙነቱ ላይ ትልቅ ፋይዳ አለው ሲል የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገለጸ። የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ እንዳለው የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ይፈታሉ መባሉ ግን በውጭ መንግስታት ተጽእኖ አይደለም ሲል አስተባብሏል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ መለስ አለም እንዳሉት የሀገሪቱ የደህንነት ምንጭ ከውስጥ ጥንካሬ የሚመነጭ ነው። ሆኖም የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት እየተወሰደ ...

Read More »

እስረኞቹን ለመልቀቅ ዝግጅት በመደረግ ላይ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 27/2010) በኢትዮጵያ ወህኒ ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ፖለቲከኞችን ለመፍታት በኢሕአዴግ ስራ አስፈጻሚ የተደረሰውን ስምምነት ተከትሎ እስረኞቹን ለመልቀቅ ዝግጅት በመደረግ ላይ መሆኑን ለስርአቱ ቅርበት ያላቸው መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ። አንዳንድ የሕወሃት ደጋፊዎች እስረኞቹን ለመፍታት የተደረሰው ስምምነትን በመቃወም ላይ መሆናቸውን ሰምተናል። የሕወሃት መሪዎችም የተወሰኑ የፖለቲካ እስረኞች እንዳይፈቱ በመከላከል ላይ መሆናቸውን ምንጮች ገለጸዋል። የኢሕአዴግ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ 18 ቀናት ያህል ባደረገው ስብሰባ እንደተወሰነ ...

Read More »