.የኢሳት አማርኛ ዜና

በባለስልጣናትና በህዝቡ አለመግባባት ሳቢያ፤ በሀዲያ የተጀመረው ስብሰባ ተቋረጠ

ጥር 30 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-እንደ ፍኖት ዘገባ፤በመልካም አስተዳደር እጦትና በመሬት ወረራ ዙሪያ በሀዲያ ዞን የተጀመረው ስብሰባ የተቋረጠው፤ መድረክ ሲመሩ በነበሩት ባለስልጣናትና በተሰብሳቢው ህዝብ መካከል በተፈጠረ አለመግባባት፤ ህዝቡ ስብሰባውን ረግጦ በመውጣቱ ነው። የክልሉ እና የዞኑ አመራሮች በተገኙበት በሆሣዕና ከተማ ባለፈው እሁድ ጥር 14 ቀን 2004 ዓ.ም በሀዲያ የባህል አዳራሽ የተጠራው ይህ ስብሰባ፤ በዞኑ ስላለው የመልካም አስተዳደር እጦትና የመሬት ወረራ ...

Read More »

የታሰሩ ወጣቶች ቁጥር መንግስት ይፋ ካደረገው እንደሚበልጥ ከእስር ቤት ያመለጠ ወጣት አጋለጠ

ጥር 29 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ባለፉት አራት ወራት የኢትዮጵያ የጸጥታ ሀይሎች የህዝብ አመጽ ለማስነሳት ይቀሰቀሳሉ ብለው የሰሩዋቸው ወጣቶች ቁጥር መንግስት ይፋ ካደረገው አሀዝ በእጅጉ እንደሚበልጥ አንድ ከእስር ቤት ያመለጠ ወጣት አጋለጠ ለደህንነቱ ሲባል ስሙን ለመግለጥ የማንፈልገው ወጣት ባለፈው ሳምንት ታስሮበት ከነበረው የታጠቅ እስር ቤት አምልጦ እንዲወጣ በተለያዩ ወገኖች ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ ነበር። ወጣቱ ከእስር ቤት አምልጦ እንደወጣ ወዲያውኑ ከኢሳት ...

Read More »

የኮንዶሚኒየም ቤቶች ለኢህአዴግ ካድሬዎችና ባለስልጣናት ዘመዶች መሰጠታቸው ቅሬታ አስነሳ

ጥር 29 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ልደታ አካባቢ የሚገኙ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ለኢህአዴግ ካድሬዎችና ባለስልጣናት ዘመዶች መሰጠታቸው ቅሬታ አስነሳ በልደታ አካባቢ በመገንባት ላይ ያሉት የኮንዶሚኒየም ቤቶች ፣ ከተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ዘግይተው ቢጠናቀቁም ሰሞኑን እየተሰራ ያለው ድራማ ግን ህዝቡን ያሳዘነ ሆኗል። የኢሳት ምንጮች እንዳሉት ኮንዶሚኒየም ቤቶቹ አስቀድመው ለገዢው ፓርቲ ካድሬዎችና የባለስልጣናት ዘመዶች ተሰጥተዋል። የአካባቢው ነዋሪ ይህን ቢያውቅም፣ የመንግስትን ይፋዊ መልስ ለመስማት በመፈለግ ...

Read More »

የአፍሪቃን መሬት የሚቀራመቱት የእርሻ ልምድና ዕዉቀት የሌላቸው ናቸው ተባለ

ጥር 29 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ለአፍሪቃዉያን ጥቅም የሚሰጥ ሳይሆን ይልቁንም ድሃ አነስተኛ ገበሬዎች የምግብ ዋስትና እንዲያጡና ከመኖሪያቸዉ እንዲፈናቀሉ የሚያደርገዉን የመሬት ቅርምትና ድርድር ከጀርባ ሆነዉ የሚያስፈፅሙት የአሜሪካን የልማት ድርጅት( USAID) ፣  የአለም ባንክና ከፍተኛ ዩኒቨርሲቲዎች መሆናቸዉን የገለፁት አሳሳቢ የፖሊሲ ጉዳዮችን በጥልቀት በማጥናት ለህዝብ በመቆም የሚሟገተዉ የኦክላንድ ኢንስቲትዩት መስራችና ዳይሬክተር አኑራ-ድሃ ሚታል ናቸዉ። ዳይሬክተሯ ይህን የገለፁት ከታዋቂዉ የቺካጎ ህዝብ ሬድዮ  ወርልድ ...

Read More »

የኢትዮጵያ ወታደሮች ከአልሸባብ ጋር ግንኙነት ፈጥረዋል ያሏቸዉን በቁጥጥር ስር አዋሉ

ጥር 29 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በሶማሊያ የኢትዮጵያ ወታደሮች  ከአልሸባብ ጋር ግንኙነት ፈጥረዋል ያሏቸዉን አምስት ሰዎች በቁጥጥር ስር አዋሉ በሶማሊያ ሂራን ክልል በበለደ-ወይን ከተማ የኢትዮጵያ ወታደሮች  ከአልሸባብ ጋር ግንኙነት እንዳላቸዉና በወታደራዊ ካምፖች ላይ የሽብር ጥቃት ሊፈፅሙ ነበር ያላቸዉን አምስት ሰዎች በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን ነዋሪዎች ገለጸዋል። ባለፈዉ እሁድ ጥዋት በከተማዉ ዉስጥ በተወሰደዉ እርምጃ በቁጥጥር ስር የዋሉት አምስት ግለሰቦች በቅርቡ በከተማዉ ዉስጥ ...

Read More »

ኢትዮጵያዊቷ በአቡ ዳቢ ሆስፒታል ለተሰጣት የማዋለድ አገልግሎት ሂሳብ መክፈል ባለመቻሏ ታገተች

ጥር 29 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በቤት ሰራተኛነት የስራ ኮንትራት ፈፅማ ዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ አቡ-ዳቢ ከገባች ከሁለት ቀን በሁዋላ በተሰማት ህመም ወደ ሆስፒታል ስትወሰድ የ9 ወር ነፍሰ ጡር ሆና በመገኘቷ የወሊድ አገልግሎት የተሰጣት ኢትዮጵያዊት የቤት ሰራተኛ የሆስፒታሉን እዳ እስካልከፈለች ድረስ እንደማትለቀቅ ገልፍ ኒዉስ የዜና ምንጭ ገለፀ። ስፖንሰር አድራጊዋና አስቀጣሪ ድርጅቷ ስለ እርግዝናዋ ምንም እንደማያዉቁና ተሰማኝ ባለችዉ የሆድ ህመም ምክንያት በስፖንሰርዋ ...

Read More »

የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አሁንም ከአረብ ሳት እንደወረደ ነው

ጥር 29 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ መንግስት ኢሳትን ለማፈን ሙከራ አድርጎ  ከአረብ ሳት እንዲወርድ ካደረገው በሁዋላ በተመሳሳይ እርምጃ የኤርትራን ቴሌቪዥን ለማፈን ባደረገው ሙከራ በአረብ ሳት የሚተላለፈው ዝግጀቱ እንዲቋረጥ መደረጉ ይታወቃል። አረብ ሳት ለኢትዮጵያ መንግስት ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ ቢቆይም፣ በማፈን ተግባሩ የቀጠለው መንግስት በአረብ ሳት የሚተላለፈው ዝግጀቱ እንዲቋረጥ ተደርጓል። የኤርትራ መንግስት ወደ ኢትዮጵያ የሚያስተላልፈው ስርጭቱ እስከ ዛሬ ሳይታፈን  ቆይቶ አሁን ለመታፈን ...

Read More »

በጋምቤላ ክልል ያለው ውጥረት በሳምንቱ መጨረሻም አይሎ ነበር ተባለ

ጥር 28 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የክልሉ ዘጋቢያችን እንደገለጠው  በምስጢር የደኅንነት አባል ሆነው ሢሰሩ  የነበሩት   አቶ ጌታቸው አንኮሬ  ባልታወቁ ሰዎች መገደላቸውን ተከትሎ  ጋምቤላ የሳምንቱ መጨረሻ ቀናትና ዛሬ በመከላከያ ሰራዊት እና በፌደራል ፖሊስ አባላት ዙሪያዋን ታጥራለች። ትናንት የፌደራል ሰራዊት አባላት በየአቅጣጫው ውጠራ አድረገው አላፊ አግዳሚውን ሲፈትሹ እንደነበር የገለጠው ዘጋቢያችን፣ በከተማው ነዋሪ ላይም ከፍተኛ የሆነ አለመረጋጋት ይታያል። የአካባቢው ባለስልጣናት በከፍተኛ ፍርሀት ውስጥ ...

Read More »

መንግስት ጥቃት ለማድረስ ሲዘጋጅ የነበረ የአልቃይዳ ህዋስ መያዟን አስታወቀች

ጥር 28 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና የፌዴራል ፖሊስ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል እንዳለው ከምሥራቅ አፍሪካ አልቃይዳ ጋር ጥብቅ ግንኙነት በመመስረት በአገር ውስጥ በማደራጀት፣ ሥልጠናና ትምህርት በመስጠት ሲንቀሳቀሱ የተደረሰባቸው ስምንት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል። የአልቃይዳ አባላቱ በአገሪቱ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በመታየት ላይ ያለውን የአክራሪነት ዝንባሌ እንደምቹ ሁኔታ ተጠቅመው ጉዳት ለማድረስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ናቸው ብሎአል ግብረሀይሉ። ተጠርጠሪዎቹ በሶማሊያ ...

Read More »

ኢሳት በሳምንቱ መጨረሻ በተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት አደረገ

ጥር 28 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢ ኤም ኤፍ ድረገጽ ስራአስኪያጅ የሆነው ዳዊት ከበደ  እንደዘገበው  በአትላንታ በተዘጋጀው ታላቅ ምሽት ላይ ቁጥሩ በብዙ መቶ የሚቆጠር ኢትዮጵያዊ ተገኝቶ ነበር። ገና ከጅምሩ በዚህ ዝግጅት ላይ አርቲስት ታማኝ በየነ፣ አርቲስት ሻምበል በላይነህ፣ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ እና ልጅ ተክሌ በክብር እንግድነት ተገኘተዋል። አርቲስት ታማኝ በየነ፣ አርቲስት ሻምበል በላይነህ፣ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ እና ተክለሚካኤል አበበ በእንግድነት ...

Read More »