ሐምሌ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የአማራ ክልል የወጣቶች ማህበር ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገለው፣ በክልሉ ውስጥ በወጣቱ ዘንድ ከፍተኛ ከበሬታ ያተረፈውና ወጣቱን ለለውጥ ለማንቀሳቀስ ከፍተኛ ስራ መስራቱ የሚነገርለት ወጣት ዘመነ ካሴ እንዲሁም የህግ ምሩቃን የመሰረቱት የአባይ ፍሬዎች ወጣቶች ማህበር ሊቀመንበር የሆነው ከፍያለው ጌጡ ከገዢው ፓርቲ የደህንነት ሰዎች ክትትል አምልጠው ወደ ሶስተኛ አገር ተሰደዋል። ወጣት ዘመነና ወጣት ከፍያለው በስደት ካሉበት ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
በጋምቤላ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነርና ሌሎች 4 ባለስልጣናት ያለመከሰስ መብታቸው ተነሳ
ሐምሌ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ባለፉት ሁለት ወራት በጋምቤላ ክልል ነዋሪዎች እንዲሁም የሼክ ሙሀመድ ሁሴን አላሙዲን ኩባንያ ሰራተኞች ላይ በተፈጸመው ጥቃት ፣ ከታጣቂዎች ጋር በመሆን ጥቃቱን አስፈጽመዋል የተባሉት የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽነር ያለመከሰስ መብታቸው በክልሉ ምክር ቤት እንዲነሳ ተደርጓል። ኮሚሽነሩ ያለመከሰስ መብታቸው ቢነሳም ዜናውን እስካጠናከርንበት ጊዜ ድረስ አለመታሰራቸው ታውቋል። የክልሉ የንግድ ቢሮ ሀላፊና ምክትላቸው ፣ የፋይናንስ ቢሮ ሀላፊዎች ...
Read More »“አገሪቷ በማን እየተመራች እንደሆነ አለመታወቁ አሣስቦኛል” ሲል መኢአድ ስጋቱን ገለጸ
ሐምሌ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በአሁኑ ጊዜ አገሪቷን እየመሩ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ናቸው መባሉ እንዳልተዋጠለት እና በትክክል ይች አገር በማን እየተመራች እንደሆነ አለመታወቁ እንዳሣሰበው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ገለጸ። ይህ የመኢአድ ስጋት የተገለጸው፤ ከፍተኛ የፓርቲው አመራሮች በጽህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ ላይ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህይወት እንደሌሉ የሚያመላክቱ ዘገባዎች እየወጡ ባሉበት ባሁኑ ጊዜ የኮሙኒኬሽን ሚኒስትሩ አቶ በረከት ...
Read More »ኢትዮጵያዊት ዲፕሎማት አደንዛዥ ዕፅ ወደ ለንደን ለማስገባት ስትሞክር ተያዘች
ሐምሌ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- “ካናቢስ”የተሰኘ አደንዛዥ ዕፅ ወደ ለንደን ለማስገባት ስትሞክር የተያዘች አንዲት ኢትዮጵያዊት ዲፕሎማት የ33 ወር እስራት ተፈረደባት። እንደ አሶሲየትድ ፕሬስ ዘገባ፤በዋሽንግተን የኢትዮጵያኤምባሲ ውስጥ የምትሠራው አመለወርቅ ወንድማገኝ የተባለች ዲፕሎማት፤ የዲፕሎማቲክ ከለላዋን በመጠቀም 56 ኪሎ ግራም የሚመዝንካናቢስ- በሄትሮን አውሮፕላን ማረፊያ በኩል ወደ ለንደን ለማስገባትስትሞክር ነው የተያዘችው። ጉዳዩን ሲከታተለው የነበረውና በምዕራብ ለንደን የሚገኘው የአይስወርዝ ክራውን ...
Read More »መንግስት አቶ መለስ ዜናዊ በህይወት መኖራቸውን በምስል አቅርቦ ማሳየት እንዳለበት ኢሳት አሳሰበ::
ሐምሌ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- መንግስት አቶ መለስ ዜናዊ በህይወት መኖራቸውን የድምጽ ወይም የቪዲዮ ምስል አቅርቦ ማሳየት እንዳለበት ኢሳት አሳሰበ:: የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ኢዲቶሪያል ቦርድ ይህን ጥያቄ ያቀረበው ዛሬ አቶ በረከት ስምኦን ኢሳት ላቀረበው ዜና የሰጡትን መልስ በማስመልከት ነው። አቶ በረከት ሪፖርተርና ሰንደቅ ለተባሉት ጋዜጦች እንዲሁም ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የኢሳትን ዜና በማስተባበል መግለጫ ሰጥተዋል። አቶ በረከት ኢሳትን ...
Read More »ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ አመታዊ ስብሰባውን በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን ገለጸ።
ሐምሌ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ከሃምሌ 22 እስከ ሃምሌ 24 ቀን 2004 ዓም ድርስ ባካሄደው የንቅናቄው አመታዊ ስብሰባ በአገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ላይ በስፋት በመነጋገር በአስቸኳይ ሊተገበሩ ይገባቸዋል ባላቸው የተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ማስተላለፉን የንቅናቄው የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለኢሳት በላከው መግለጫ አስታውቋል። የመለስ ዜናዊ አገዛዝ ላለፉት 21 አመታት የተገበራቸው የዘረኝነት ፖሊሲዎች ...
Read More »የፍትህ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ማእከላዊ ምርመራ ቀርቦ ቃሉን ሰጠ::
ሐምሌ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ጋዜጠኛ ተመስገን በፌስ ቡክ ገጹ ባሰፈረው ማስታወሻ፦ በዛሬው ዕለት ማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ተጠርቶ፦” ፍትህ ሚኒስቴር ክስ ስላቀረበብህ ቃልህን ስጥ”መባሉን ገልጿል። ከቀናት በፊት የታገደቸው ጋዜጣ ትለቀቅና ለንባብ ትውላለች ብሎ ሢያስብ፣ እሱ እና ባልደረቦቹ ባልነበሩበትና ባልተከራከሩበት ችሎት ቀርባ ‹‹ትወረስ›› የሚል ወሳኔ እንደተላለፈባት ተመስገን አስታውሷል። “ ካዛስ ምን ይሆናል?የተወረሰችውን ጋዜጣ መንግስት ሸጦ ገቢውን ይወስዳልን? ...
Read More »መንግስት የግል ትምህርት ቤቶችን መውረሱን አመነ::
ሐምሌ ፳፮ (ሀያ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- በአዲስ አበባ የሚገኙ ከ102 በላይ የግል ትምህርት ቤቶች መወረሳቸውን መንግስት አምኖአል። ኢሳት ከወራት በፊት፣ ራሳቸውን ማስተዳዳር የሚችሉ ትምህርት ቤቶች ወደ መንግስት እንደዞሩ ዘገባ በሰራበት ወቅት፣ መንግስት ዜናውን ሲያስተባብል ነበር። ይሁን እንጅ የአዲስ አበባ መስተዳዳር ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ ከ102 በላይ ትምህርት ቤቶች ወደ መንግስት መዞራቸውን ገልጧል። መንግስት በትምህርት ቤቶች ውስጥ የዘረጋውን የአንድ ...
Read More »የአለማቀፍ ግጭት ተንታኝ ቡድን ባለስልጣናት አቶ መለስ ዜናዊ አርፈዋል ይላሉ::
ሐምሌ ፳፭ (ሀያ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- የአለማቀፍ ግጭት ተንታኝ ቡድን ባለስልጣናት አቶ መለስ ዜናዊ አርፈዋል ይላሉ: ድርጅቱ በበኩሉ ዜናውን አስተባብሎአል ኢሳት የአለማቀፍ ግጭት ተንታኝ ቡድን በእንግሊዝኛው አጣራር አይ ሲ ጂ የውስጥ ጥናትና የዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡን በመጥቀስ አቶ መለስ ዜናዊ ማረፋቸውን መዘገቡ ይታወሳል። ይህንን ተከትሎ ተቋሙ በዛሬው እለት ማስተባበያ ያወጣ ሲሆን፣ በማስተባበያውም ፣ ተቋም የአቶ መለስ ዜናዊን የጤና ...
Read More »የኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅት ከመንግስት የድርድር ጥያቄ እንደቀረበለት ገለጠ::
ሐምሌ ፳፭ (ሀያ አምስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- የድርጅቱ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የሆኑት አቶ ሀሰን አብዱላሂ ለኢሳት እንደገለጡት፣ ግንባሩ እስካሁን ድረስ ከመንግስት ጋር ድርድር ያላደረገ ቢሆንም፣ በኬንያ መንግስት በኩል የንግግር ጥያቄ እንደቀረበለት ተናግረዋል። የኦጋዴን ነጻ አውጭ ድርጅት ድርድሩ በገለልተኛ አገር መካሄድ እንዳለበት፣ አለማቀፍ ኮሚኒቲው ድርድሩን እንዲመራ ቅድመ ሁኔታ ማስቀመጡን አቶ ሀሰን ገልጠዋል:: ከብዙ ጊዜ ውይይት በሁዋላ ከመንግስት የቀረበውን ...
Read More »