በህውሀት የብቸኝነት እዝ የሚመራው የኢትዮጵያ ሰራዊት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ከሚደረጉ ህዝባዊ ትግሎች ጎን እንዲሰለፍ ጥሪ ቀረበ

ታህሳስ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ የትግል አቅጣጫውንና የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ባወጣው መግለጫ እንዳመለከተው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትና የደህንነት ሀይሎች ለመንግስት ህዝብን የመጨቆኛ መሳሪያ መሆናቸውን አቁመው ከህዝብ ጎን እንዲቆሙ ጥሪውን አስተላልፎል:: ህውሀት ኢህአዴግ በህዝባችን ላይ የሚያደርሰው በደልና ግፍ ሊያበቃ ይገባል ያለው የሸንጎ መግለጫ በእስር ላይ ያሉት የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ባስቸኮይ እንዲፈቱም መንግስትን አሳስቦል:: አፋኝ ...

Read More »

አዲስ ራዕይ የተሰኘ መጽሄት በሁሉም የመንግስት መ/ቤት ሰራተኞች ዘንድ በግዳጅ እየተሸጠ ነው

ታህሳስ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በሞቹ የቀድሞ ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ የስራ ታሪክ ዙሪያ የሚያጠነጥን አዲስ ራዕይ የተሰኘ መጽሄት በሁሉም የመንግስት መ/ቤት ሰራተኞች ዘንድ በግዳጅ በ 100 ብር እየተሸጠ መሆኑ ተገለጸ:: ከሀገር ቤት የኢሳት ምንጮች እንደገለጡት በጠ/ሚሩ ህይወት ዙሪያ የሚያጠነጥነውን አዲስ ራዕይ የተሰኘ መጽሄት ከ 2000 ብር በላይ ደሞዝተኛ የሆነ በአንድ ክፍያ 100 ብር ለመግዛት ይገደዳል ከ2000 ብር በታች ...

Read More »

አቶ በረከት ስምአን ተጽእኖቸው አየቀነሰ የህዋሃት ጡንቻ አየፈረጠመ መምጣቱ ተገለፀ

ታህሳስ ፲፭(አስራ አምስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስተር መለሰ  ዜናዊ ማለፋቸውን ተከትሎ በኢትዮጵያ ፖለትካ መድረከ ውስጥ  ሚናቸው ጎልቶ የነበረው አቶ በረከት ስምአን ተጽእኖቸው አየቀነሰ የህዋሃት ጡንቻ አየፈረጠመ መምጣቱ ተገለጸ:: የአረና ትግራይ አመራር አባል የሆኑት አቶ አስራት አብርሃም የውስጥ ምንጮችን ጠቅሰው ባሰራጩት ጹሁፍ አንዳመለከቱት አቶ በረከት ስለ ኤርትራ የስጡት መግለጫ  ህዋሃትን አሰተባብሮባቸዋል:: አቶ በረከት ስምኦን የኤርትራ ተቃዋሚዎች ፖልቶክ መድረክ ...

Read More »

የባህርዳር ሹማምንት በከፍተኛ ሙስና ተዘፍቀዋል ተባለ

ኢሳት ዜና:-ለአቶ በረከት ስምኦን የተጻፈ ሚስጢራዊ ደብዳቤ እንዳመለከተው በባህርዳር ከተማ ከንቲባ በአቶ ፋንታ ደጀን አማካኝነት በርካታ ወንጀሎች እየተፈጸሙ ናቸው። ደብዳቤው በብአዴን ውስጥ ሁለት በጥቅም የተሳሰሩ ቡድኖች መፈጠራቸውን ያመለክታል። አንደኛው ቡድን ደጀኔ ሽባባው በተባለው የብአዴን ጽሀፈት ቤት ሀላፊ የሚመራ ሲሆን በዚህ ቡድን ውስጥ የገቢዎች ጽህፈት ቤት ሀላፊ የሆነው ክብረት ሙሀመድ፣ የከተማ አግልገሎት የቴክኒክ ዘርፍ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ፍቅር መኮንን፣ የቤቶች ...

Read More »

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ነገ ድምፃቸውን ያሰማሉ

ኢሳት ዜና:-<<ከፓትርያርክ ምርጫ በፊት እርቅና ሰላም ይቅደም>>በሚል መሪ ሀሳብ የ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በመጪው እሁድ ከቅዳሴ በሁዋላ የተቃውሞ ድምፃቸውን እንዲያሰሙ ጥሪ ቀረበ። ደጀ ሰላም እንደዘገበው ላለፉት 20 ዓመታት በውግዘት የተለያዩ አባቶች አንድ እንዲሆኑ፣ አንዲት ቤተ ክርስቲያን፣ አንድ አስተዳደርና አንድ ቅ/ሲኖዶስ እንዲኖር ለማድረግ ሲካሄድ የሰነበተው የእርቀ-ሰላም ሂደት በመልካም ውጤት ሊጠናቀቅ ጫፍ ላይ በደረሰበት ጊዜ፤ የታየውን የተስፋ ጭላንጭል በሚያዳፍን መልኩ ...

Read More »

የብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች አድማ በመቱ ማግስት- መንግስት ለተጫዋቾቹ ጥያቄ ምላሽ እንደሚሰጥ ቃል ገባ

ኢሳት ዜና:-ከ 31 ዓመታት በሁዋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ያለፉትና በመጪው ጥር ወር በደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ውድድር የተሻለ ውጤት ያስመዘግባሉ ተብለው ተስፋ የተጣለባቸው የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን አባላት ከክፍያና ከአንዳንድ ጥያቄዎች ጋር በተያያዘ አድማ የመቱት ከጥቂት ቀናት በፊት ነበር። ዋልያዎቹን  አድማ ለመምታት ያነሣሳቸው፤ ቀደም ካለ ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ድረስ በእግር ኳስ ፌዴሬሽኑ በኩል  የተደረገላቸው ምንም ዓይነት ድጋፍ አለመኖሩ፤እንዲሁም  በሽልማት ...

Read More »

ሰበር ዜና: የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል ተመሰረተ

የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል ተመሰረተ ህዝባዊ ሀይሉ በወጣቶችና ምሁራን የተመሰረተ ነው ተብሎአል ወያኔን በኃይል የማስወገድ፤ ሁሉንም ሀይሎች ያሳተፈ ሰላማዊና ዲሞክራሲ የሥልጣን ሽግግር በሃገሪቱ እንዲኖር እንደሚታገል አስታውቋል ህዝባዊ ሀይሉ በዶ/ር ብርሀኑ ነጋ ከሚመራው   የግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ጋር ያለው ግንኙነት በግልጽ የታወቀ ነገር የለም::

Read More »

ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ በላይ ኢህአዴግ ሆኖብናል ሲሉ ተቃዋሚዎች ገለጹ

ታህሳስ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-መጪው የአካባቢና የአዲስ አበባ ምርጫ ፍትሀዊ መሆን አለበት በማለት ፔትሺን ተፈራርመው ያስገቡት 33 የፖለቲካ ድርጅቶች ዛሬ በመኢአድ ጽህፈት ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ፣ ምርጫ ቦርድ ለጥያቄያቸው መልስ አለመስጠቱን ገልጸው፣ በንባብ የሰጡዋቸውን ምላሽ እንደ አንድ ትልቅ መንግስታዊ ተቋም በደብዳቤ ለመግለጽ እንኳን ፈቃደኛ አልሆኑም ፣ ምርጫ ቦርድ ከኢህአዴግ በላይ ኢህአዴግ ሆኖብናል ብለዋል። የፓርቲዎች ጥምረት ...

Read More »

የባለስልጣናት የሃብት ምዝገባ መረጃ ከሕዝብ እንደተደበቀ ነው

ታህሳስ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በፌዴራል የሥነምግባርና ጸረሙስና ኮሚሽን ሥር የሚገኘው የባለሥልጣናት የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችን ሃብትና ንብረት ለመመዝገብ የተቋቋመው ቢሮ እስካሁን የ50ሺ ባለስልጣናትን ሃብት መመዝገቡን ሰሞንን በመንግስት መገናኛ ብዙሃን ቢገልጽም የአንዳቸውንም የሃብት መረጃ ለሕዝብ ይፋ እንዳላደረገ ምንጮች አስታወቁ፡፡ በሃብት ማሳወቅና ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 668/2002 መሰረት የተቋቋመው ይህው ቢሮ የመንግስት ባለስልጣናትና ተሿሚዎችን ሃብትና ንብረት በመመዝገብና በማደራጀት ለሕዝብ ይፋ ማድረግና ...

Read More »

አቶ አንዱአለም አራጌ ላለፉት 15 ወራት በጨለማ ቤት ታስረዋል

ታህሳስ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊ/መንበርና የህዝብ ግንኙነት ሐላፊ የሆነው አቶ አንዱዓለም አራጌ በጨለማ ቤት ውስጥ ታስሮ፣ ቀዝቃዛ መሬት ላይ እንዲተኛ መደረጉ በየጤናው ላይ ከፍተኛ ችግር እየፈጠረበት መሆኑን ትናንት ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ተናግሯል። አቶ አንዱዓለም የመተንፈሻ ችግር እንዳለባቸው ይሁን እንጅ በጠባብ ክፍል 6 ሆነው በመታጎራቸው መታመማቸውንና ከባለቤታቸውና ጥቂት ቤተሰባቸው ውጪ ሌሎች ጓደኞቻቸውና የስራ ባልደረቦቻቸው ...

Read More »