በተውለደሬ ወረዳ አንድ ጠበቃ በክርክር በማሸነፋቸው በቀበሌው ባለስልጣናት ተደበደቡ

ታህሳስ  ፳፫(ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በደቡብ ወሎ በተውለደሬ ወረዳ አቶ አበራ ካሳ የተባሉ ጠበቃ ከቀበሌው ሊቀመንበር ጋር በመሬት ጉዳይ ላይ ሲያደርጉት የነበረውን ክርክር በፍርድ ቤት ማሸነፋቸውን ተከትሎ ፣ ሊቀመንበሩ ደጋፊዎቻቸውን አስተባብረው ጠበቃው እንዲደበደቡ አድርገዋል፡፡ ጠበቃውም  በደረሰባቸው ከፍተኛ ድብደባ ሆስፒታል ገብተዋል። የመሬቱ ባለቤት አቶ አስፋው ሽበሺ የሚባሉ አርሶአደር ሲሆኑ ፣ የቀበሌው 01 እና 02 ሊቀመንበሮች መሬቱን ለግላቸው ለማድረግ ተደጋጋሚ ...

Read More »

በኩዌት አንድ ኢትዮጵያዊት ሞታ ተገኘች

ታህሳስ  ፳፫(ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-አረብ ታይምስ እንደዘገበው ኢትዮጵያዊቷ የሞተቸው ከቀጣሪዋ ድርጅት መስኮት ላይ ዘላ በመውደቅ ሳይሆን አይቀርም። ሰራተኛዋ በራስ ቅሏ አካባቢ ከፍተኛ ደም ፈሷት እንደሞተች የህክምና ባለሙያዎች ገልጸዋል። በግቢው ውስጥ ሌሎች ሶስት ኢትዮጵያዊያን ሰራተኞች እንደነበሩ ቢገለጽም ኢትዮጵያውያኑ የቤት ሰራተኛዋ በምን ሰበብ እራሱዋን እንዳጠፋች እንደማያውቁ ገልጸዋል።

Read More »

በአማራ ክልል 500 ፖሊሶች ስራቸውን ለቀቁ

ታህሳስ  ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ለኢሳት የደረሰው መረጃ እንዳመለከተው በክልሉ በአንድ አመት ውስጥ ብቻ 500 ፖሊሶች ስራቸውን ለቀዋል። ፖሊሶች ስራቸውን መልቀቃቸውን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር በአንድ ስብሰባ ላይ አምነዋል። ፖሊሶች ስራቸውን የለቀቁት በአስተዳደር ጫና እና ከስራቸው ጋር የማይጣጣም እና የኑሮ ውድነቱን ለማቋቋም የማያስችል ክፍያ ስለማይከፈላቸው መሆኑን ይገልጻሉ። በክልሉ ውስጥ የሚታየው የኑሮ ውድነት ፖሊሶችን ብቻ ሳይሆን አጠቃላይ የመንግስት ሰራተኞችን ...

Read More »

በደሴ መስኪዶች በሀይል እየተነጠቁ ነው

ታህሳስ  ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የተለያዩ የመንግስት አካላት ከፖሊስ ጋር በመተባባር በደሴ የሚገኙ መስኪዶችን ቁልፎች አዳዳስ ለተመረጡት የመጅሊስ አመራሮች እንዲያስረክቡ ማድረጋቸው  ታውቋል። በዛሬው እለት በከተማ የሚገኙ ዋና ዋና መስኪዶች ቁልፎች ለአዳዲሶቹ የመጅሊስ ተመራጮች እንዲረከቡዋቸው ተደርጓል። በተመሳሳይ ዜናም የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን በሙስሊም መሪዎች ቤት ውስጥ ሆን ብሎ በማስቀመጥ  ቪዲዮ እየተሰራ መሆኑንና ቪዲዮውም አመራሮችን ለመክሰስ እንደማስረጃ እንደሚቀርብ ታውቋል። በመንግስት እና ...

Read More »

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰሙ

ታህሳስ  ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ተማሪዎቹ ባለፈው አርብ ምሽት በጀመሩት ተቃውሞ የመማሪያ ክፍሎች መስኮቶች መሰባበራቸውን ለማወቅ ተችሎአል። አረብ ምሽትና ቅዳሜ የፌደራል ፖሊስ አባላት ዩኒቨር  ስቲውን መቆጣጠራቸውን ተከትሎ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው የወጡ ሲሆን ገሚሶቹ በቤተክርስቲያኖች ውስጥ ተጠልለው እንደነበር ታውቋል። ተማሪዎቹ ተቃውሞአቸውን ያሰሙት አዲሱን የውጤት አሰጣጥ ፖሊሲ በመቃወም እንዲሁም መሰረታዊ የሆኑ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ስላልተሟሉላቸው ነው። በግቢው ውስጥ 2 ሺ ...

Read More »

የጎንደር ዩኒቨርስቲ የተማሪዎች ዲን ተማሪዋን አስገድደው ደፈሩ

ታህሳስ  ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የተማሪዎች ዲን የሆኑት አቶ ናትናኤል ህዳር 27 ቀን 2005 ዓ,ም የሚያስተምሯትን ተማሪ ስልክ በመደወል ከምሽቱ 1፡30 ገዳማ ቢሯቸው ድረስ ካስጠሩ በኋላ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል እንደፈጸሙባት ከጎንደር ያገኘነው ዜና ያስረዳል። የተደፈረችው ተማሪ በግሏ ጥረት ወደ ዩኒቨርስቲው ሆስፒታል በመሄድ አስፈላጊውን የህክምና ምርመራ ያደረገች ሲሆን የምርመራው ውጤትም ተማሪዋ የአስገድዶ መደፈር ሰላባ መሆኗን የሚያረጋግጥ ነው። ተማሪዋን አስገድደው ...

Read More »

የአረና ፓርቲ ጽህፈት ቤት በዶዘር ፈረሰ

ታህሳስ  ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በሁመራ የሚገኘው የፓርቲው ጽህፈት ቤት በዶዘር እንዲፈርስ ከተደረገ በሁዋላ የድርጅቱ ጽህፈት ቤትም ተዘርፎአል። በተመሳሳይ መንገድም የድርጅቱ አባል የሆኑት የአቶ ገብረእግዚ ናዩ ቤት ያለምንም ማስጠንቀቂያ እንዲፈርስ ተደርጓል። በተንቤን የድርጅቱ አባል የሆኑት አቶ ጸጋየም መታሰራቸው ታውቋል። በአቶ ገብሩ አስራት በሚመራው አረና ፓርቲ ላይ የትግራይ ክልል ባለስልጣናት የሚወስዱት እርምጃ እየከፋ መምጣቱን መዘገባችን ይታወሳል።

Read More »

አቶ ጁነዲን ሳዶ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለፓርላማ መቅረቡ ተገለጠ

ታህሳስ  ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነታቸውና ከኢህአዲግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነታቸው የተባረሩት አቶ ጁነዲን ሳዶ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ የሚጠይቅ ደብዳቤ ለፓርላማ መቅረቡ ተገለጠ:: ሪፖርተር ጋዜጣ በሮብ እትሙ የምክር ቤቱ የቅርብ ምንጮቹን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው አቶ ጁነዲን ሳዶ በፓርላማ የስነስርአት ደንብ መሰረት ሊጠየቁበት የሚችል የህግ ጉዳይ ሊኖር ስለሚችል በም/ቤቱ አባልነታቸው ያገኙትን ያለመከሰስ መብት ም/ቤት እንዲያነ ሳ በመንግስት ...

Read More »

የተቃዋሚ 33 የፓለቲካ ድርጅቶች ያቆቆሙት ጊዚያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድን ሊከሰው መሆኑን አስታወቀ

ታህሳስ  ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- የምርጫ  ቦርድ ከፍተኛ ሀላፊ የኢህአዴግ አባል ሆነው ለክልልምምክር ቤት አባልነት ምርጫ መወዳደራቸውንም አጋልጦል:: ጊዜዊ ኮሚቴው ለምርጫ ቦርድ ባቀረበው 18 ጥያቄዎች ማስረጃ ያላቸውን ይፋ ያደረገ ሲሆን ምርጫ ቦርድን ለፓርላማ አፈጉባኤ እንደሚከስ አስታውቆል:: የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በአስተባባሪ ኮሚቴው የቀረቡት 18 ጥያቄዎች ማስረጃ የላቸውም ብሎ ጥያቄዎቹን ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ ነው ወሳኝ ያላቸው ማስረጃዎች ለሀገር ውስጥና ...

Read More »

ሽምግልናውን ሲያካሒድ ከነበሩ አስታራቂዎች የቤተክርስትያን ኣባቶች መካከል ኣንደኛው ከኢትዮጲያ ሲባረሩ ሁለተኛው የደረሱበት ኣይታወቅም

ታህሳስ  ፳፪(ሃያ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኣዲስ ኣበባዎቹ ተደራዳሪ ኣባቶች ባለፈው ሳምንት ያወጡት መግለጫ ተገደው የፈረሙበት መሆኑም ተገለጸ።በቅርቡ በዳካስ ቴክሳስ የረካሄደውን ሶስተኛ ዙር በሶሳንጀለሰ ካሊፎርንያ ለማካሔድ ቀጠሮ ይዘው ከተነሱት ኣባቶች ኣንደኛው የሆኑት ብጹነ ብጹነ ኣቡነ ገሪማ በገጠማቸው የጤና ችግር ኣሁንም በዮኤስ ኣሜሪካ አንደሚገኙ ለማወቅ ተችሉኣል።ቅዳሜ ታህሳስ 20/2005 ኣሜሪካ የደረሱት ሊቀ ካህናት ኃይለሰላሴ ኣለማየው ታግደው መባረራቸውን ለሾይስ ኦፍ ኣሜሪካ የአማርኛ ...

Read More »