የፖሊዩ ቫይረስ በሺታ በኢትዩጵያ እና ሶማሊያ በወረርሺኝ መልክ መከሰቱን የጤና ጥበቃ ሚንስቴር አስታወቀ።

መስከረም ፳፫(ሃያ ሦስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፖሊዩ ቫይረስ በተከሰተበት አካባቢ ሳይታወቅ ጉደት አድርሶዋል፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናት በበሺታው መጠቃታቸውን በሚኒስቴሩ የእናቶችና ህጻናት ጤና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ በቀለ ለጋዜጠኖች ተናግረዋል፡፡ በሐገራችን ኢትዩጵያ እና አጎራባች አገሮች የተከሰተውን የፖሊዮ በሽታ ወረርሽኝ ለመከላከል በአገር አቀፍ ደረጃ እድሜያቸው ከ5 አመት በታች ለሆኑ ህጻናት የፖሊዩ ቫይረስ መከላከያ ክትባት መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል። መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ...

Read More »

በባህርዳር ድሆች መኖሪያ ቤታቸውን እየተቀሙ ለጎዳና ተዳዳሪነት ተዳርገዋል

መስከረም ፳፪(ሃያ ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የድሃ ድሃ ተብለው ተመርጠው ኑሮቸውን በጉስቁልና የሚመሩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከደርግ ጊዜ አንስቶ እስካሁን ድርስ በቀበሌ ቤቶች ሲገለገሉ ቢቆይም ያለ አግባብ በባለስልጣናት እየተቀሙ መሆኑ ለከፍተኛ ችግር እንዲጋለጡ እንዳደረጋቸው ነዋሪዎቹ ለኢሳት ገልጸዋል። የመንግስት ባለስልጣናት ደሀዎችን “ተተኪ ቦታና ቤት ይሰጣችሁዋል” በማለት ቤቶችን እየቀሙ ለባለሐብቶች እና ለራሳቸው በሊዝ እየገዙ አዳዲስ ህንጻዎችን መገንባታቸውን ተከትሎ ድሆች ጎዳና ላይ ...

Read More »

በአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን መስሪያ ቤት ውስጥ የሚታየው የንብረት ውድመትና ሙስና አስከፊ ነው ተባለ

መስከረም ፳፪(ሃያ ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከፍተኛ ገንዘብ ወጥቶባቸው በተዝረከረከ የንብረት አስተዳደር ሥርዓት ምክንያት ለብክነት፣ ለምዝበራ እና ለብልሽት የተጋለጡ ንብረቶችን ለመታደግ ትክክለኛ የአሰራር ስርዓት መጥፋቱን፣ የመስሪያ ቤቱ ባለስልጣናትም ያለጠያቂ በሙስና መዘፈቃቸውን  የፌድራል የስነ ምግባር እና የጸረ ሙስና ኮሚሺን ገለጸ፡፡ በአዲስ አበባ ውሃና ፍሳሽ ባለስልጣን ውስጥ የDCI እና የDN  የቧንቧ መገጣጠሚያዎች ቁመታቸው እና ውፍረታቸው በናሙና እየተለካ ሌሎች መመዘኛዎች ግን ...

Read More »

ካራቱሬ 62 ሚሊዮን ብር የንግድ ባንክን እዳ አለመክፈሉ ተዘገበ

መስከረም ፳፪(ሃያ ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በጋምቤላ ክልል ከ300 ሺ ሄክታር ያላነሰ መሬት በነጻ በሚባል ዋጋ የተረከበው የህንዱ የእርሻ ኩባንያ ካራቱሬ ፣ በተሰጠው መሬት ላይ የልማት ስራ አለማከናወኑንና የባንክና ሌሎች እዳዎችን ለመክፈል አለመቻሉን ሰንደቅ ጋዜጣ ዘግቧል። በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተጠባባቂ የቢዝነስ ዴቭሎፕመንት የስራ ሒደት ባለቤት የሆኑት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ለጋዜጣው  እንዳስረዱት ፣ ካራቱሪ ከባንኩ እ.ኤ.አ በዲሴምበር 2011 ወደ ...

Read More »

በአዲስአበባ ከሚገኙ 58 የአሸከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማት ብቃት ያላቸው 10 ብቻ ናቸው

መስከረም ፳፪(ሃያ ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንገድና ትራንስፖርት ቢሮ ቢሮው በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የአሸከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋማት ላይ ያደረገውን ግምገማ ውጤት ተከትሎ ማንኛውም የመንጃ ፈቃድ ሰልጣኝ ከጥቅምት1 ቀን 2006 በፊት በማናቸውም የአሸከርካሪዎች ማሰልጠኛ ተቋማት ውስጥ ትምህርት እንዳይጀምሩ አስጠነቀቀ፡፡ ዛሬ ይፋ በተረደገው የጥናት ውጤት መሰረት ከ58 የማሰልጠኛ ተቋማት ዝቅተኛውን መስፈርት ማሟላት የቻሉት 10 ያህሉ ብቻ ...

Read More »

በአርባምንጭ እስር ቤት ታስረው ከተፈቱት 39 ሰዎች መካከል 14ቱ ዛሬ የስራ ስንብት ደብዳቤ ደረሳቸው

መስከረም ፳፩(ሃያ አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በቁጫ ከወራት በፊት የነተሳውን ተቃውሞ መርታችሁዋል በሚል 40 ሰዎች በአርባምንጭ እስር ቤት ታስረው ከቆዩ በሁዋላ ፍርድ ቤት እንዲፈቱ ቢያዝም ፖሊስ አልፈታም በማለቱ ሰዎቹ ለተጨማሪ ወራት ከታሰሩ በሁዋላ ከቀናት በፊት መፈታታቸው ይታወቃል። ይሁንና የመንግስት ሰራተኞች ወደ ስራ ገበታቸው ለመመለስ ወደ መስሪያ ቤታቸው ሲያቀኑ ለ14ቱ የስራ ስንብት ደብዳቤ ተሰጥቷቸዋል። ከስራ ከተሰናበቱት መካከል አቶ ቲንኮ ...

Read More »

መብራት ሀይል በምዝበራና በብልሹ አሰራር ከ1 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ማባከኑን ጸረ ሙስና ኮሚሽን በጥናት አረጋገጠ

መስከረም ፳፩(ሃያ አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጸረ ሙስና ኮሚሽን  በአዲስ አበባ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ውስጥ ስላለው የንብረት አስተዳደር አሰራር ስርዓት ጥናት አካሒዶ ከፍተኛ የገንዘብ ጉድለት መገኘቱን አረጋግጧል። በጥናቱ የተለየው የመጀመሪያው ችግር እቃዎች ተገዝተው ወደ ንብረት ክፍል ከመግባታቸው በፊት ንብረት ክፍሉን ቅድመ ዝግጅት እንዲያደረግ የሚያስችለውና ወጥነት ያለው የማሳወቂያ ስርዓት አለመሰራት ነው፡፡ አብዛኛዎቹ ግዥዎች ከተፈጸሙ በኋላ ለእቃ ግምጃ ቤቶች ወጥነት ...

Read More »

የኢህአዴግ ባለስልጣናትን የሚያስተምረው ትምህርት ቤት ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር ውዝግብ ውስጥ ገባ

መስከረም ፳፩(ሃያ አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በፕሮፌሰር ባደግ በቀለ የሚመራውና የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናትን በተለይም የአመራር ሥልጠናዎችን በአገር ውስጥ በማስተማር የሚታወቀው ኢንተርናሽናል ሊደርሺፕ ኢንሰቲትዩት  በትምህርት ሚኒስቴር ስር ካለው የከፍተኛ ትምህርት አግባብነት ጥራት ኤጀንሲ ጋር ውዝግብ ውስጥ መግባቱ  ታውቋል። የሁለቱ አካላት ውዝግብ መነሻ ምክንያቱ ተቋሙ ሳይፈቀድለት በዶክትሬት ዲግሪ ከፍተኛ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር በመጀመሩ ነው፡፡ የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ ኢንስቲትዩት ሳይፈቀድለት ...

Read More »

የአሜሪካ የመንግስት መስሪያቤቶች በበጀት ውዝግብ ምክንያት በከፊል ተዘጉ

መስከረም ፳፩(ሃያ አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዩናይትድ ስቴትስ አስተዳደር የሪፐብሊካን እና የዲሞክራቲክ ፓርቲ አባላት በአዲሱ በጀት ላይ ስምምነት ላይ ባለመድረሳቸው ሳቢያ  በርካታ መስሪያ ቤቶችና  ተቋማት በከፊል እየተዘጉ ነው።  ሪፐብሊካኑ የምክር ቤት አባላት በጀቱን ለማጽደቅ  የፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ   የህክምና ፖሊሲ ማሻሻያ፤ በእግሊዝኛው አጠራር “ሄልዝ ኬር ሪፎርም” ሊዘገይ ይገባል  የሚል አቋምን እንደ ቅድመ-ሁኔታ አስቀምጠዋል። በዚህም ምክንያት በፌዴራል መስሪያ ቤቶችና በልዩ ልዩ ...

Read More »

ኢሳት ያዘጋጀው የመኪና የቶምቦላ እጣ በፈረንጀች አቆጣጠር ኦክቶበር 11 ታዛቢዎች በተገኙበት በአምስተርዳም ከተማ ይወጣል።

መስከረም ፳፩(ሃያ አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በየአገሩ የተመደቡ የትኬት ሽያጭ ወኪሎች የተሸጡና ያልተሸጡ ቁጥሮችን በመለየት እስከ ኦክቶበር 8፣ በስልክ ወይም በኢሜል እንድታስታውቁ እንጠይቃለን። ትኬቱን እስካሁን ያልገዛችሁ ውድ የኢሳት ቤተሰቦችና ደጋፊዎች የቀሩትን ጥቂት ቀናት በመጠቀም ከአካባቢያችሁ ካሉ ወኪሎች ወይም በኦን ላይን ትኬቶችን መግዛት የምትችሉ መሆኑን ለማስታወስ እንደወዳለን። ትኬቶችን ሽጣችሁ የጨረሳችሁ ደግሞ በኢሳት አካውንት ገንዘቡን ገቢ እንድታደረጉ እናሳስባለን ኢሳት ቶምቦላ ሽያጭ ...

Read More »