በአማራ ክልል ቴሌቪዥን ጋዜጠኞች እና አመራሮች መካከል መተማመን እንደሌለ ጋዜጠኞች ተናገሩ

ጥቅምት ፳፭(ሃያ አምስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአማራ ክልል ጋዜጠኞች እና በፖለቲካ ታማኝነት ተሹመው በሚያገለግሉ መሪዎች መካከል መተማመን የለም ሲሉ ጋዜጠኞች ለኢሳት ተናግረዋል፡፡ በጋዜጠኞች እና በአመራሩ መካከል ለተፈጠረው ልዩነት በርካታ ምክንያቶች ቀርበዋል። ጋዜጠኞቹ ለክልሉ ቴሌቪዥን ስርጭት ልዩ ምልክት ወይም ሎጎ ሁኖ እንዲያገለግል የተመረጠው የሰማእታት ሃውልት አርማ የአማራን ህዝብ የሚወክል አይደለም በማለት ተቃውሞ እያሰሙ ነው፡፡ በአመራሮች በኩል በሚታየው ከባድ የሙስና ...

Read More »

በኢህአዴግ ላይ እምነት እያጣ የመጣውን እና ተቃውሞውን በመግለጽ ላይ ያለውን አርሶ አደር ለማፈን አዲስ የስልጠና መርህ ተግባራዊ እየተደረገ ነው፡፡

ጥቅምት ፳፭(ሃያ አምስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመላው ኢትዩጵያ ተግባራዊ እንዲደረግ በኢህአዴግ ጽ/ቤት በኩል ለ14 ቀናት የሚቆይ ሰልጠና ተቀርጾ ወደ ታች በመውረድ ተግባራዊ እየተደረገ ነው፡፡ ቅድሚያ እንዲያስተገብር ትዕዛዝ የተላለፈለት የአማራ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ለሚገኙ አርሶ አደሮች ስልጠናውን እየሰጠ ነው። ስልጠናው የኢትዩጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ  ወይም ኢህአዴግ የተጋድሎ ታሪክ  ላይ የሚያተኩር ሲሆን አርሶ አደሮች በኢህአዴግ ላይ ተቃውሞ እያሰሙ በመምጣታቸው ስልጠና ...

Read More »

በግንባታ እቃዎች ላይ የሚታየው የዋጋ ንረት ዘረፉን እየጎዳው ነው

ጥቅምት ፳፭(ሃያ አምስት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በ ግንባታ ዘርፍ በየጊዜው እየናረ የመጣው የግብአቶች ዋጋ ንረት በተለይ በብድር የሚሰሩ በርካታ ግንባታዎችን እያስተጓጎለ እንደሚገኝ ታውቋል። ከመንገዶች ባለስልጣን የተገኘ መረጃ እንዳመለከተው የግንባታ ግብአቶች ዋጋ ባለፉት አምስት ዓመታት ብቻ ከ100 እስከ 237 በመቶ የዋጋ ንረት አሳይቶአል፡፡ መረጃው እንደአብነት ከዘረዘራቸው ግብአቶች መካከል ነዳጅ እ.ኤ.አ በ2009 ዓ.ም በሊትር 7.13 ብር የነበረው እ.ኤ.አ በ2013 ወደ 16.91 ብር ...

Read More »

ኦህዴድ በግምገማ እየተናጠ ነው

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ኦህዴድ ከወረዳ ጀምሮ ያሉ አባላቱን እየገመገ ሲሆን፣ ግምገማው በእርስ በርስ ሽኩቻና መጠላላፍ እየተካሄደ ነው። ከድርጅቱ አመራሮች መካከል አንዱ ለኢሳት እንደገለጹት ድርጅቱ ህልውና አደጋ ውስጥ ወድቋል።የዝምድና አሰራር እንዲሁም በቡድን ተደራጅቶ አንዱ ሌላውን የሚያጠቃበት ሁኔታ በሰሞኑ ግምገማ በስፋት የታየ ሲሆን፣ አብዛኛው ከታች እስከ ላይ ያለው አመራር በሙስና የተዘፈቀ በመሆኑ አንዱ ...

Read More »

በአቶ መለስ ሞት የውጭ ምንዛሬ እጥረት ተፈጥሮ እንደነበር አይኤም ኤፍ ገለጸ

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አለማቀፉ የገንዘብ ተቋም ባወጣው የ2004-2005 ግምገማ ኢትዮጵያ ድህነትን ለመቅረፍ የምታደርገውን ጥረት አድንቋል። በኢኮኖሚው ረገድ ስኬት እየታየ መሆኑን፣ አገሪቱም የ7 በመቶ እድገት ማስመዝገቡዋን የገለጸው አይ ኤም ኤፍ፣ የዋጋ ግሽበትን ለመቆጣጠር መንግስት የወሰደውን እርምጃንም አድንቋል። የአቶ መለስ ሞት በፈጠረው መደናገጥ ሁሉም የውጭ ምንዛሬ ለመግዛት መገደዱን በዚህም ሳቢያ የተፈጠረው የምንዛሬ እጥረት ተጽኖ መፍጠሩን ገልጿል። የግሉ ...

Read More »

በሶማሊ ክልል የሚከበረው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በአል ፌዝ ነው ሲሉ ነዋሪዎች ተናገሩ

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በክልሉ ለረጅም አመታት ኖረው በተለያዩ ምክንያቶች ከአካባቢው እንዲለቁ የተደረጉ አንዳንድ ሰዎች ለኢሳት እንደገለጹት ፣ መስተዳድሩ እንኳንስ የሌሎችን አካባቢዎች ህዝብ መብት ለማክበር ቀርቶ የክልሉን ነዋሪዎች መብት ማክበር አልቻለም ብለዋል። ከሌላ ክአካባቢዎች የመጡ በተለይም የአማራ ተወላጆች ሶማሊያ መናገር አትችሉም እየተባሉ ከስራ መባረራቸውን የገለጹት እኝህ ነዋሪዎች፣ በንግድ ስራ የሚተዳደሩና በጅጅጋ ቁልፍ የገበያ ቦታዎችን እና ቀበሌ ...

Read More »

አዲሱ ሌተናንት ጄኔራል በመቶ ሚሊዮን ብር የሚቆጠር ሀብት እንዳላቸው ታወቀ

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ ሌተናንት ጄኔራል ሆነው የተሾሙት በሱዳን የሚገኘውን እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስር በመሆን  በጸጥታ መስከበር ስራ ላይ የተሰማራውን የኢትዮጵያ ጦር የሚመሩት ምናልባትም ጀኔራል ሳሞራ የነሱን ሊተኩ ይችላሉ የሚባሉት ሌተናንት ጀኔራል ዮሀንስ ገብረመስቀል ተስፋማርያም በአዲስ አበባ የገነቡዋቸው የንግድ ህንጻዎች በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዋጋ እንደሚያወጡ ለእርሳቸው ቅርብ የሆኑ ሰዎች ገልጸዋል። ጀኔራሉ ባለፈው አመት መጋቢት ...

Read More »

የፓኪስታን የታሊባን መሪ ተገደለ

ጥቅምት ፳፪(ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሀኪሙላ መሱድ የሚባለው የፓኪስታን ታሊባን መሪ የተገደለው በአሜሪካ ሰው አልባ የጦር ጅቶች መሆኑን አለማቀፍ ሚዲያዎች ቢዘግቡም እስካሁን ከአሜሪካ መንግስት በኩል የተሰጠ ማረጋገጫ የለም። ግለሰቡ በአሜሪካ ከሚፈለጉ አሸባሪዎች ማካከል አንዱ ነው። አሜሪካ ግለሰቡ ያለበትን ለጠቆመ 5 ሚሊዮን ዶላር ለመስጠት ቃል ገብታ ነበር። የመሱድ ምክትል ባለፈው ግንቦት ወር በተመሳሳይ መንገድ መገደሉ ይታወሳል። የፓኪስታን መንግስት ...

Read More »

በባህርዳር ከተማ ከፍተኛ ፍተሻ እየተካሄደ ነው

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምክንያቱ በውል ባይታወቅም ካለፉት 4 ቀናት ጀምሮ በከተማዋ ከፍተኛ ፍተሻ እየተካሄደ እንደሆነ የዘጋብያችን መረጃ ያመለክታል። በተለይ ዛሬ በከተማዋ መውጫና መግቢያ በሮች ላይ ሰዎች ከመኪናዎች እና ባጃጆች ላይ እንዲወርዱ እየተደረገ በጥብቅ ተፈትሸዋል። አንዳንድ ወገኖች  መንግስት ጸረ ሰላም እና አሸባሪዎች በከተማዋ ገብተዋል የሚል ወሬ እንደሚያስወራ ሲገልጹ፣ ሌሎች ነዋሪዎች ደግሞ የከተማውን ህዝብ ለማስበረገግ ሆን ብሎ ...

Read More »

በኮንዶሚኒየም ቤት ግንባታ የቻይና ኩባያዎች ሊሰማሩ ነው

ጥቅምት ፳፩(ሃያ አንድ )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዓመት 50ሺ የኮንዶምኒየም ቤቶችን ለመገንባት የያዘው ዕቅድ ከባድ ትችትን ያስከተለበት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዓመት ከ 100ሺ በላይ የቤቶች ግንባታ ለማከናወን ፊቱን ወደቻይና ኩባንያዎች ማዞሩ ተሰማ፡፡ አስተዳደሩ ከ800ሺ በላይ የኮንዶምኒየም ፣ ከ 136 ሺ በላይ የ40 በ60 ቤት ፈላጊ ነዋሪዎችን የመዘገበ ሲሆን ከዚህ ፍላጎት ጋር በማይጣጣም መልኩ በዓመት 50ሺ ቤቶች ገደማ ለመስራት ...

Read More »