Amsterdam

በደንቢያ የቻይና የመንገድ ስራ ድርጅት እንደገና ወደ ካምፑ እንዲገባ ከተደረገ በሁዋላ በደረሰ ሁለተኛ ጥቃት ተመልሶ ወጣ

መጋቢት ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በደንቢያ ወረዳ ጎርጎራ አካባቢ በሚገኘው የቻይና ካምፕ ላይ በአካባቢው የሚንቀሳቀሱት ሃይሎች ያደረሱትን ጥቃት ተከትሎ ኩባንያው ሰራተኞችንና መኪኖችን ወደ ቆላ ድባ ካስወጣ በሁዋላ፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የመከላከያ ሰራዊት ወደ አካባቢው በመጓዝ አካባቢውን ማረጋጋቱን በመግለጽ፣ ኩባንያው ወደ ቦታው እንዲመለስ ቢያደርግም፣ ዛሬ አርብ በደረሰ ተጨማሪ የቦንብ ጥቃት ተሽከርካሪዎች እንደገና አካባቢውን ለቀው ወጥተዋል። ከፍተኛ የመከላከያ ...

Read More »

የጃፓን መንግስት በሶማሊያ ክልል ለድርቅ ለተጠቁ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች የሚውል የ2 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ለዩኒሴፍ ለገሰ።

መጋቢት ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የገንዘብ እርዳታው በዩኒሴፍ አማካኝነት ለውሃ፣ ለጤና፣ ለንጽህና አገልግሎቶች፣ ለተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት እና ለአጣዳፊ የጠቅማጥ በሽታ መድሃኒት መግዣ እንደሚውልም ተገልጿል። ድርቁን ተከትሎ ተላላፊ በሽታዎች በመዛመታቸው በአካባቢው ያሉ ነዋሪዎችን ሕይወት ለመታደግ ለንጽህና አገልግሎት 1.5 ሚሊዮን ዶላር ተመድቧል።የኢትዮጵያው ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ባቀረቡት አፋጣኝ የእርዳታ ጥያቄ ...

Read More »

በደንቢያ ወረዳ የሚታየውን ተቃውሞ ተከትሎ አንድ ቤተክርስቲያን በወታደሮች ተቃጠለ

መጋቢት ፳፰ (ሃያ ስምንት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት እንደገለጹት በሰሜን ጎንደር ዞን በደንቢያ ወረዳ ጩሃይት ከተማ መጋቢት 26 ቀን 2009 ዓም ጀሪ ደበርጋ ጊዮርጊስ የተባለ ቤተክርስቲያን በአካባቢው በሰፈሩ ወታደሮች ተቃጥሏል። ህዝቡ በድርጊቱ በመቆጣት ተቃውሞውን ሲያሰማ ወታደሮች ድርጊቱን የፈጸሙት የአርበኞች ግንቦት 7 አባላት ናቸው በማለት ህዝቡን ለማሳመን ቢሞክሩም ፣ ነዋሪዎች ግን አልተቀበሉትም። ወታደሮቹ ድርጊቱን የፈጸሙት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ ...

Read More »

በወሎ ለእርዳታ የመጣ እህል መዘረፉን ነዋሪዎች ተናገሩ በሙስና እና በአስተዳደር ችግር የተማረሩት ዜጎች መንግስት አለ ወይ ሲሉ ይጠይቃሉ።

መጋቢት ፳፰ (ሃያ ስምንት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው ሳምንት በወሎ በተደረገው ስብሰባ ለእርዳታ የተላከ እህል፣ ዘይት፣ ክክ እና ሌሎችም ነገሮች እየተዘረፉ መሆኑን የሚናገሩት አቶ አለባቸው አረጋ፣ ሰራተኞች በሞቱ ሰዎች ሳይቀር እየፈረሙ ገንዘብ ይወስዳሉ ይላሉ። ነዋሪዎቹ 100 ኩንታል የእርዳታ ስንዴ በባለስልጣናት መዘረፉንም ይገልጻሉ ። ልማት የለም የሚሉት አቶ አለባቸው፣ ስኳር እና ዘይት ካየን 5 ወራት አልፎናል ብለዋል። መሬት በአምቻ ...

Read More »

በመላው አገሪቱ በሚገኙ ወረዳዎች መብራት የለም በሚባልበት ደረጃ ላይ መደረሱን መረጃዎች አመለከቱ

መጋቢት ፳፰ (ሃያ ስምንት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር የተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ከህዝብ ያሰባሰቡትን መረጃ አጠናክረው የላኩትን መረጃ በማድረግ በጻፈው ደብዳቤ በመላ አገሪቱ የሚታየው የመብራት መቆራረጥ ህዝቡን ተስፋ አስቆርጦታል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ጽ/ቤት ፣ በፓርላማ አባላት አማካኝነት ከህዝብ ያሰባሰባቸውን 66 ገጽ ጥያቄዎችን ለውሃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስቴር የላከ ሲሆን፣ ጥያቄዎቹ በአብዛኛው በመብራት መቆራረጥ፣ ...

Read More »

በአፋር የመንግስት ሰራተኞች ያለፈቃዳቸው ለብሄር ብሄርሰቦች በአል በሚል ግማሽ ደሞዛቸው ተወሰደባቸው

መጋቢት ፳፰ (ሃያ ስምንት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የመንግስት ሰራተኞች ለኢሳት እንደገለጹት ለበአሉ በሚል ደሞዛቸው ያለፈቃዳቸው መቆረጡን ካወቁ በሁዋላ፣ አቤቱታ ማሰማታቸውን ተከትሎ በአዋሽ አርባ ዞን የጤና ባለሙያዎችን ማክሰኞ መጋቢት 26 ቀን 2009 ዓም በመስብሰብ ለማወያየት ቢሞክሩም ፣ ሰራተኞች ግን ድርጊቱን በመቃወም አልተቀበሉትም። በዚህ የተበሳጩት ባለስልጣናት እናንተ ፈቃደኞች ሆናችሁም አልሆናችም ደሞዛችሁ ይቆረጣል በማለት የእብሪት መልስ ሰጥተዋል። ዛሬ መጋቢት 28 ደግሞ ...

Read More »

በሰሜን ጎንደር ዞን በደንቢያ የሚገኘው የቻይና ኩባንያ በድርጅቱ ላይ የደረሰውን ጥቃት ተከትሎ ከአካባቢው ለቆ ወጣ

መጋቢት ፳፯ (ሃያ ሰባት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በዚያው በደንቢያ የሚሊሺያ ሃላፊው ህዝቤን መሳሪያ አላስገፍፍም በማለት ራሱን አጥፍቷል። ለኢሳት የአካባቢው ነዋሪዎች እንደገለጹት የአርሶአደሩን መሬት ያለበቂ ካሳ በመንጠቅ እንዲሁም በሰራተኞች ላይ በደል በማድረስ በሚታወቀው ጎርጎራ አካባቢ በሚገኘው የቻይና ካምፕ ላይ መጋቢት 25 እና 26 በተፈጸመው ጥቃት 3 ሰዎች መገደላቸውን እና በበርካታ ተሽከርካሪዎች ላይ ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ ፣ የመንገድ ስራ ድርጅቱ ...

Read More »

በቀድሞው የምርጫ ቦርድ ምክትል ሃላፊ የሚመራው የሰብአዊ መብት ድርጅት በቂሊንጦ የደረሰው የእሳት አደጋ ሆን ተብሎ በእስረኞች የተነሳ ነው አለ

መጋቢት ፳፯ (ሃያ ሰባት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ራሱን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ብሎ የሚጠራው እና በህወሃት አባሉ በቀድሞው የምርጫ ቦርድ ምክትል ሊ/መንበር ዶ/ር አዲሱ ገ/እግዚአብሄር የሚመራው ድርጅት በዛሬው ዕለት ለፓርላማው ፍትህ እና አስተዳደር ጉዳዮች ቆሚ ኮሚቴ ባቀረበው ሪፖርት፣ የእሳት አደጋው እንዲነሳ ያደረጉት በከፍተኛ ወንጀል ተጠርጥረው የፍርድ ሂደቱን የሚጠባበቁ እስረኞች ናቸው በማለት የፖሊሲን መረጃ አጠናክሯል። የኮሚሽኑ ኮምሽነር ዶ/ር አዲሱ ...

Read More »

በኦጋዴን በተከሰተ የኮሌራ ወረሽኝ ከመቶ በላይ ዜጎች ሕይወታቸውን ማጣታቸውን የኦጋዴ ብሄራዊ ነጻነት ግንባር አስታወቀ

መጋቢት ፳፯ (ሃያ ሰባት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- እንደ ግንባሩ መግለጫ በምስራቅ ኢትዮጵያ ኦጋዴን አካባቢ በጥቂት ቀናት ውስጥ እየተዛመተ በመጣው የኮሌራ ተላላፊ በሽታ ምክንያት ከመቶ በላይ ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። በተለይ የዶሎ፣ ቆራሄ፣ ኖጎቦ፣ ጃራር እና አፍዴር ወረዳዎች ክፉኛ ተጠቅተዋል። ከኮሌራው ወረሽኝ በሽታው በተጨማሪ በቀጠናው እየተስፋፋ የመጣው መጠነ ሰፊ የድርቅ አደጋ በነዋሪዎቹ ላይ ከፍተኛ ሰባአዊ ቀውስ እያስከተለ ቢሆንም ዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ...

Read More »

በኢትዮጵያ በምግብ አለመመጣጠን ችግር የተነሳ በየዓመቱ ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ 53 በመቶ ሕጻናት እንደሚሞቱ ተነገረ፡፡

መጋቢት ፳፯ (ሃያ ሰባት)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- 23 በመቶ የሚደርሱ እናቶች የደም ማነስ ችግር እንዳለባቸውና ይህም ችግር በወሊድ ወቅት እስከሞት ለሚደርስ አደጋ እየዳረጋቸው መሆኑ ተሰምቷል፡፡ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የተገኘ መረጃ በምግብ አለመጣጠን ሳቢያ ገና በእናታቸው ማህጸን እያሉ ጀምሮ በህጻናት ላይ የጤና ችግሮች ሊከሰት እንደሚችል ይናገራል፡፡ ከጤና ችግሮቹ መካከል የሕጻናት ሞት፣ በተደጋጋሚ በበሽታ መጠቃት እና ከታመሙ በሁዋላ በቶሎ ማገገም ...

Read More »