.የኢሳት አማርኛ ዜና

እነ አቶ መላኩ ፈንታ ተከላከሉ ተባሉ

ሚያዚያ ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፌዴራል የፀረ ሙስና ኮሚሽን በቀድሞ የጉምሩክ ኃላፊ በነበሩት አንደኛ ተከሳሽ አቶ መላኩ ፈንታውና ግብረ አበሮቻቸው ላይ ከተከሰሱባቸው አስራ ሰባት ክሶች በተወሰኑት የጥፋተኝነት ብይን አስተላልፎባቸዋል። 1ኛ ተከሳሽ አቶ መላኩ ፈንታ የኢትዮጵያ ገቢዎች እና ጉምሩክ ባለስልጣን የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር፣ 2ኛው ተከሳሽ አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ የባለስልጣኑ የህግ ማስከበር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር፣ 3ኛው ተከሳሽ አቶ ...

Read More »

ዱባይ 6ቱን የኢትዮጵያ ነጋዴዎች ክስ አነሳች

ሚያዚያ ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ባለፈው የካቲት ወር በዱባይ የተደረገውን የምግብ ኤግዚቢሽን ለመካፈል ያቀኑ 6 የኢትዮጵያ ነጋዴዎች፣ የተበላሸ ስጋ አቅርበዋል በሚል ለሁለት ወራት ያክል ከአገር እንዳይወጡ ታግተውና ሁለቱ ነጋዴዎች ደግሞ በተደጋጋሚ ሲታሰሩ መቆየታቸውን ተከትሎ ቤተሰቦቻቸው ጭንቅት ውስጥ መግባታቸውን በተደጋጋሚ ከገለጹ በሁዋላ፣በዩናይትድ አረብ ኤምሬትስና በኢህአዴግ መንግስት መካከል በተደረገ ስምምነት፣ ክሳቸው መነሳቱ ወደ አገራቸው መሄድ እንደሚችሉ እንደተፈቀደላቸው ታውቋል። ነጋዴዎቹ ...

Read More »

የውጭ ምንዛሪ ያስገኛሉ ተብለው በመንግስት ድጋፍ ሲደረግላቸው የቆዩ ኩባንያዎች ውጤታማ አይደሉም ተባሉ

ኢሳት (ሚያዚያ 19 ፥ 2008) የውጭ ምንዛሪ እንዲያስገኙ ታስበው በመንግስት ልዩ የማበረታቻ ድጋፍ ሲደረግላቸው የቆዩ ከ30 በላይ ኩባንያዎች በየወሩ ስድስት ሚሊዮን ዶላር እንዲያስገኙ ቢጠበቅባቸውም ከ90 ሺ ዶላር በታች ማስመዝገባቸው ተገለጠ። በጉዳዩ ቅሬታ የተሰማቸው የመንግስት ባለስልጣናት በበኩላቸው ድርጅቶቹ ሲደረግላቸው የቆየ ልዩ ልዩ ድጋፍ ተቋርጦ በኩባንያዎቹ ላይ ምርመራ እንደሚካሄድ አሳስበዋል። እነዚሁ በብረታ-ብረትና በኤሌክትሮኒክስ ማምረት ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙት ድርጅቶች ለምርት ግብዓት የሚሆናቸውን ...

Read More »

በአፍሪካ ሃገራት የመገናኛ ብዙህን ነጻነት እያሽቆለቆለ መምጣቱን አንድ ጥናት አመለከተ

ኢሳት (ሚያዚያ 19 ፥ 2008) ኢትዮጵያን ጨምሮ በበርካታ የአፍሪካ ሃገራት የመገናኛ ብዙህን ነጻነት እያሽቆለቆለ መምጣቱን በጉዳዩ ዙሪያ ጥናትን ያደረገ አንድ አለም አቀፍ ተቋም ረቡዕ ይፋ አደረገ። መቀመጫውን በዚህ በአሜሪካ ያደረገውና የ2015 ሪፖርቱን ለህዝብ ይፋ ያደረገው ፍሪደም ሃውስ (Freedom House) እኤአ አቆጣጠር በ2015 የአለም የመገናኛ ብዙሃን ባለፉት 12 አመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ አሽቆልቁሎ መገኘቱን አስታውቋል። ከአፍሪካ ቡሩንዲ፣ በመገናኛ ብዙሃን ላይ ...

Read More »

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ አዲሱ ትውልድ የኢትዮጵያን አንድነት እንዲጠብቅና የታሪክ ህፀፆችን እንዲያርም ጥሪ አቀረበ

ኢሳት (ሚያዚያ 19 ፥ 2008) የኢትዮጵያ አንድነት የመጠበቅና የታሪክ ህፀፆችን ማረም ከአዲሱ ዘመንት ዲሞራቶች ይጠበቃል ሲል ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ገለጸ። ታዋቂው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ “ የዘንድሮ ግንቦት 20” በሚል ርዕስ ሰሞኑን ከወህኒ ቤት ለመገናኛ ብዙሃን በላከው ፅሁፍ ኢህአዴግ ወደስልጣን የመጣበትን 25ኛ አመት በማስመልከት ያለፉትን 50 አመታት የኢትዮጵያ ፖለቲካዊ ሁኔታ በመገምገም ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ እንደሚያስፈልግ አስገንዝቧል። በኢትዮጵያ ተማሪዎች ትግል ውስጥ የነበረው ...

Read More »

አቶ ኦኬሎ አኳይን ጨምሮ ሰባት ተከሳሾች እስከ ዘጠኝ አመት የሚደርስ ጽኑ እስራት ተፈረደባቸው

ኢሳት (ሚያዚያ 19 ፥ 2008) የቀድሞ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የነበሩት አቶ ኦኬሎ አኳይን ጨምሮ ሰባት ተከሳሾች በተመሰረተባቸው የሽብርተኛ ወንጀል ክስ ከሰባት እስከ ዘጠኝ አመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ። ተከሳሾች የቀረበባቸውን ወንጀል እንዳልፈጸሙ በመግለጽ የመከላከያ ማስረጃን በማቅረብ ሲከራከሩ ቢቆዩም ፍርድ ቤቱ ተከሳሾች ያቀረቡት ማስረጃ የሚያስተባብል አይደለም ሲሉ ውድቅ ማድረጉም ታውቋል። የተከሳሾች ጉዳይ ሲመለከት የቆየው ፍርድ ቤቱ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ርዕሰ ...

Read More »

ተመድና የኢትዮጵያ መንግስት በጋራ ለምግብ እርዳታ ገቢ የማሰባሰብ ዘመቻ ጀመሩ

  ኢሳት (ሚያዚያ 19 ፥ 2008) በኢትዮጵያ ለአስቸኳይ ጊዜ የምግብ እርዳታ ለተጋለጡ ሰዎች የሚያስፈልገው ድጋፍ በበቂ ሁኔታ አለመገኘቱን ተከትሎ የተባበሩት መንግስታት ድርጅቶችና መንግስት በለጋሽ ሃገራት በመዘዋወር ገቢ የማሰባሰብ ዘመቻ ጀመሩ። ይኸው ማክሰኞ በኖርዌይ መዲና ኦስሎ ከተማ የተጀመረው ድጋፍን የማሰባሰብ ዘመቻው በስዊዘርላንድ ጄኔቫና በዚህ በአሜሪካ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና መቀመጫ በሆነችው የኒውዮርክ ከተማ እንደሚካሄድም ታውቋል። ከ10 ሚሊዮን ለሚበልጡ ተረጂዎች ወደ 1.4 ...

Read More »

ዜጎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ወደ አዲስ አበባ መፍለሳቸውን ቀጥለዋል

ሚያዚያ ፲፱(አሥራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ ገቢ የሚያገኙና በምእራባውያን የአኗኗር ዘዴ የሚኖሩ ጥቂት ግለሰቦች የመኖራቸውን ያክል፣ ተገኘ የሚባለው የኢኮኖሚ እድገት የዘለላቸው ወይም ፈጽሞ ያላያቸው እጅግ በርካታ ዜጎች ስደትን እንደአማራጭ በመውሰድ ባህር እና በረሃ አቋርጠው ወደ አረብ አገራት ወይም ወደ አውሮፓና አሜሪካ ሲሰደዱ ብዙዎች ህይወታቸውን አጥተዋል። ጉልበቱ የሌላቸው አቅመ ደካሞች ደግሞ ወደ ዋና ዋና የክልል ...

Read More »

በአዲስ አበባ ስራቸውን የሚለቁ ፖሊሶች ቁጥር ከመቼውም ጊዜ በላይ ጨምሮአል

ሚያዚያ ፲፱(አሥራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሚሰሩት ስራ ክብደት አንጻር የሚከፈላቸው ክፍያ ህይወታቸውን በአግባቡ ለመምራት እንዳላስቻላቸው የሚናገሩት ፖሊሶች፣ በገዢው ፓርቲ በኩል መፍትሄ ባለማግኘታቸው ስራቸውን ለቀው በመውጣት ላይ ናቸው። የፖሊስ እጥረት ያጋጠመው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የቅጥር ማስታወቂያ ቢያወጣም የሚመዘገብለት ሰው አላገኘም። አንድ ፖሊስ ለኢሳት ወኪል ሲናገር፣ ከእርሱ ጋር ሰልጥነው ከተቀጠሩት ከ2 ሺ 300 ፖሊሶች መካከል ግማሽ የሚሆኑት ...

Read More »

ሰመጉ በጋምቤላ ለጠፋው የሰው ህይወትና ለወደመው ንብረት መንግስትን ተጠያቄ አደረገ

ሚያዚያ ፲፱(አሥራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ ባወጣው ጋዜጣው መግለጫ፣ ከ200 በላይ ንጹሃን ዜጎች ለተገደሉበት ከ100 በላይ ዜጎች ለቆሰሉበትና በርካታ ህጻናትና ሴቶች ተጠልፈው ለተወሰዱበት ድርጊት ፣ መንግስትን ግንባር ቀደም ተጠያቂ አድርጓል። ከደቡብ ሱዳን የሚመጡ ታጣቂዎች ተደጋጋሚ ግድያና ዝርፊያ እየፈጸሙ መሆኑ እየታወቀ፣ የአካባቢው ነዋሪዎች ራሳቸውንና ንብረታቸውን የሚከላከሉበትን መሳሪአ በመንግስት እንዲፈቱ መደረጉ አንድ ጥፋት መሆኑን ...

Read More »