.የኢሳት አማርኛ ዜና

ከኦነግ ጋር በመሆን የሽብር ተግባር ለመፈጸም ተንቀሳቅሰዋል በተባሉት ስዎች ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የእስር ቅጣት አስተላለፈባቸው

ኢሳት (መጋቢት 19 ፥ 2009) የፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) በመሆን የሽብር ተግባር ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ ውለዋል ተብለው ለእስር ከተዳረጉ 21 ሰዎች መካከል 16ቱ ከአራት እስከ 13 አመት በሚደርስ ፅኑ ዕስራት እንዲቀጡ ማክሰኞ ወሰነ። ተከሳሾቹ በአዲስ አበባና በሶስት የኦሮሚያ ክልል ዞኖች ነዋሪዎች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፣ ሁሉም ግለሰቦች የሃገሪቱን ህዝቦች አንድነት የማፈራረስና የኦሮሚያ ክልልን ከፌዴሬሽኑ የመገንጠል አላማ ይዘው ተንቀሳቅሰዋል ...

Read More »

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ተከትሎ ለእስር ከተዳረጉት ውስጥ 5 ሺ የሚሆኑት ክስ ሊመሰርትባቸው መሆኑ ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 19 ፥ 2009) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተግባራዊ መደረግን ተከትሎ ለእስር ከተዳረጉ ከ20ሺ በላይ ሰዎች መካከል አምስት ሺ የሚሆኑት ክስ ሊመሰርትባቸው መሆኑ ተገለጸ። በጥቅምት ወር በሃገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተቀሰቀሰውን ህዝባዊ አመጽ ለመቆጣጠር ተግባራዊ የተደረገውን ይህንኑ አዋጅ ምክንያት በማድረግ 26ሺ 130 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው እንደነበር የአዋጁን አፈጻጸም የሚከታተለው ኮማንድ ፖስት ይፋ አድርጓል። አዲስ አበባ ከተማን ጨምሮ በተለያዩ ክልሎች ለእስር ...

Read More »

በመገንባት ላይ ያሉና በቀጣይ የሚገነቡ የባቡር መስመሮች ከግንባታ እስከ ማስተዳደር ያለው ስራ ለውጭ ሃገር ኩባንያ እንዲሰጥ መንግስት ወሰነ

ኢሳት (መጋቢት 19 ፥ 2009) የኢትዮጵያ መንግስት ያጋጠመውን የፋይናንስ የብድር አቅርቦት ችግር ተከትሎ በመገንባት ላይ ያሉና በቀጣይ የሚገነቡ የባቡር መስመሮች ከግንባታ እስከ ማስተዳደር ያለው ስራ ለውጭ ሃገር ኩባንያ እንዲሰጥ ወሰነ። በዚሁ አዲስ ስምምነት መሰረትም የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የሞጆ-ሃዋሳ-አርባ ምንጭ-ሞያሌ የባቡር መስመር ግንባታ እና አስተዳደርን ለውጭ ሃገር ኩባንያ ለመስጠት የሚያስችል የመግባባቢያ ሰነድ መፈረሙን ሰኞ ይፋ አድርጓል። ኮርፖሬሽኑ የባቡር መስመር ግንባታዎችን ...

Read More »

ህዝባዊ ተቃውሞው የበጀት እጥረት ፈጥሮብናል ዋጋም አስከፍሎናል ሲሉ አመራሮች ተናገሩ

መጋቢት ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በኦሮምያና በአማራ ክልሎች ተነስቶ በነበረው ህዝባዊ ተቃውሞ የተነሳ ወረዳዎች ስራ መስራት አቁመው ትኩረታቸውን ሁሉ ተቃውሞውን ወደ መከላከል አድርገው እንደነበረና ይህንን ተቃውሞ ለመቆጣጠር ለወረዳዎች የተበጀተውን በጀት በማጥፋታቸው ከፍተኛ የበጀት እጥረት መከሰቱን የተለያዩ አመራሮች ተናግረዋል። የፐብሊክ ሚኒስቴር ሃላፊዎች ከክልል አመራሮች ጋር በተወያዩበት ወቅት እንደተገለጸው፣ የክልሎች ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮዎች እስከ ወረዳ የሚደርሱ 31 ...

Read More »

የፈረንሳይ የልማት ተራድኦ ቆሸን ለመለወጥ ለአዲስ አበባ መስተዳደር ገንዘብ ሰጥቶ እንደነበር ተዘገበ

መጋቢት ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ብሎምበርግ ባወጣው ዘገባ የፈረንሳይ የልማት ተራድኦ እኤአ በ2011 በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በቆሻሻ ናዳ ያለቁበትን ረጲ የቆሻሻ መድፊያ ወይም በተለምዶ ቆሸን ለመዝጋት ለአዲስ አበባ መስተዳደር 34 ሚሊዮን 600 ሺ ዩሮ መስጠቱን ገልጿል። ገንዘቡ የቆሻሻ መድፊያውን ለመዝጋትና ከአካባቢው ለሚነሱ ዜጎች መልሶ መቋቋሚያ ታስቦ የተለገሰ ነበር። በቆሸ የደረሰው አደጋ ፖለቲካዊ መሆኑን የዘገበው ጋዜጣው፣ የፈረንሳይ ...

Read More »

ኩማ ደመቅሳ በጀርመን የሚኖሩ የሃይማኖት አባቶች የዲያስፖራውን ተጽእኖ የሚቀንስ ስራ እንዲሰሩ ጠየቁ

መጋቢት ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በጀርመን የኢትዮጵያ አምባሳደር ኩማ ደመቅሳ ባለፈው የሳምንቱ መጨረሻ ቀናት በጀርመን የሚኖሩ የሃይማኖት አባቶች እንዲሁም ከገዢው ፓርቲ ጋር ቀረቤታ ያላቸውን ነጋዴዎችና ግለሰቦች በመሰብሰብና ከፍ ያለ ግብዣ በማድረግ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በአገሪቱ ላይ የሚያደርሱትን ተጽእኖ ለመቋቋም የሚያስችል ስብከት እና ሌሎችንም ስራዎች እንዲሰሩ አዘዋል። ቅዳሜ ቀን ለሃይማኖት አባቶች ብቻ በተዘጋጀው ዝግጅት ላይ ከኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን፣ ...

Read More »

በፊንላንድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ አባላት ለቴንፐር ኮሌጅ የተቃውሞ ደብዳቤ ጻፉ

መጋቢት ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በፊላንድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የቴንፐር ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ለአቶ ኃ/ማሪያም ደሳለኝ ሊሰጥ የታሰበውን የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሽልማት በማውገዝ ለዩንቨርሲቲው አስተዳደር ደብዳቤ አስገብቷል። በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣውን አፈና፣ ድግያ፣ የሰብዓዊ መብት ረገጣ ከሚዘውረው የህወሃት ኢህአዴግ ፓርቲ ባለስልጣናት ውስጥ በዋናነት በጠቅላይ ሚንስትርነት የሚመሩት አቶ ኃ/ማሪያም ደሳለኝን በቀጣዩ ግንቦት ወር 2017 እ.ኤ.አ. ለመሸለም ማቀዱ ...

Read More »

የእንግሊዝ መንግስት ለአንባገነን አገራት መሳሪያ መሸጡን እንዲያቆም ሲሉ የአገሪቱ ዜጎች ጠየቁ

መጋቢት ፲፱ (አሥራ ዘጠኝ)ቀን ፪፲፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የእንግሊዝ መንግስት ዜጎቻቸውን ለሚጨቁኑ፣ሰብዓዊ መብቶችን ለሚጥሱ አንባገነን መንግስታት መሳሪያ መሸጡን እንዲያቆም ሲሉ ”የመሳሪያ ሽያጩ ፍትሃዊ ይሁን’ የሚል መፈክር ያነገቡ ሰላማዊ ሰልፈኞች ተይንተ ሕዝብ አካሄደዋል። ጸረ ጦርነት ባነሮችን የያዙት ሰልፈኞች የእንግሊዝ መንግስት አፋኝ ለሆኑት አገራት ኢትዮጵያ፣ ሳኡዲ አረቢያ፣ ባሕሬን እና ቬንዙዌላን ለመሳሳሉ አንባገነኖች መሳሪያ በመሸጥ ሰላማዊ ዜጎችን ከማስጨፍጨፍ ሚናውን እንዲታቀም ሲሉ ጠይቀዋል። ...

Read More »

በእስራዔል የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባንዲራ ያወረደው ማስተዋል ጥላሁን በነጻ ተለቀቀ

ኢሳት (መጋቢት 18 ፥ 2009) በእስራዔል ተላቪቭ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ በመግባት ባንዲራ ያወረደውና ምልክቱን ያቃጠለው ኢትዮጵያዊ በፍድ ቤት በነጻ ተለቀቀ። ድርጊቱ ሲፈጸም በኢትዮጵያ የነበሩት አምባሳደር ጸጋዬ በርሄ የደህንነት ስጋት አለብኝ በማለት ለፍርድ ቤቱ ያቀረቡት አቤቱታ ተቀባይነት አላገኘም። ሆኖም ተከሳሽ ኢትዮጵያዊ ከኤምባሲው 500 ሜትር እንዲርቅ ውሳኔ ተላልፎበታል። ሃሙስ መጋቢት 14, 2009 በእስራዔል ቴላቪቭ ወደ ሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በመግባት ባንዲራውን በማወረድ የኮከብ ...

Read More »

መንግስት ከቆሼ መደርመስ ለተረፉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ምንም ድጋፍ አላደረገም ተባለ

ኢሳት (መጋቢት 18 ፥ 2009) በአዲስ አበባ በቆሻሻ ክምር መደርመስ የተረፉት ከ325 በላይ ነዋሪዎች በመንግስት በኩል የተደረገላቸው ምንም አይነት ድጋፍ እንደሌለ ገለጹ። በቆሻሻ ክምር ናዳው እናቱን፣ አባቱን፣ እህቶቹን፣ አያቱን ጨምሮ 7 ቤተሰቦቹን ያጣው ወጣት አስረስ እውነቱ ለኢሳት እንደገለጸው ከአደጋው የተረፉትና በአካባቢው ያሉት በመቶዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች አካባቢውን እንዲለቁ በመንግስት ታዘዋል። ይህም ሆኖ አካባቢውን ሲለቁ መንግስት መጠለያም ሆነ መቋቋሚያ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆኑን ...

Read More »