ግንቦት ፳፩ ( ሃያ አንድ ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከ3 ቀናት በፊት በአምባሳደር ሽፈራዉ ጃርሶ የሚመራው ኢምባሲ ከፍተኛ ወጪ በማዉጣት ደቡብ ኮሪያ ዋና ከተማ ዉስጥ በሚገኘው ባለ 5 ኮከብ ሎቴ ሆቴል ያዘጋጀው ዝግጅት በአገሪቱ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ እንዳጋጠው ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ኢምባሲው የሚስጥር ጥሪ ወረቀት መላኩንና እንግዳ ሆነው የተገኙት የህወሃት አባላት ብቻ መሆናቸውን የሚገለጹት ኢትዮጵያውያን፣ በግብዣው ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
ከመቀሌ አቻው ጋር ጨዋታ ያደረገው የባህር ዳር ከነማ ክለብ ጥፋተኛ ተብሎ ቅጣት ተፈረደበት
ኢሳት (ግንቦት 17 ፥ 2009) ከመቀሌ አቻው ጋር ሲጫወት በመቀሌ ደጋፊዎች ተደብድቦ ወደ አማራ ክልል የተመለሰው የባህርዳር ከነማ እግር ኳስ ክለብ ጥፋተኛ ተብሎ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቅጣት ተጣለበት። የባህር ዳር ከነማ ክለብ በረኛን ጨምሮ 4 ተጫዋቾች በቀይ ካርድ ተባርረው በ7ቱ ብቻ ወደ መቀሌ ሄዶ ደጋፊ በሌለበት ዝግ ስታዲየም ጨዋታው ከተቋረጠበት ጊዜ ጀምሮ ያለው 16 ደቂቃዎች ከመቀሌ አቻው ጋር ውድድር ...
Read More »የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው ላይ የአንድ አመት ከስድስት ወር የእስር ቅጣት በየነ
ኢሳት (ግንቦት 18 ፥ 2009) የፌዴራሉ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ሰሞኑን የጥፋተኝነት ብይን በተላለፈበት ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው ላይ የአንድ አመት ከስድስት ወር የእስር ቅጣር አርብ ሰጠ። ጋዜጠኛው የተላለፈበት የ 18 ወር እስራት ከእስር ቆይታው ጋር የሚቀረረብ በመሆኑ ተከሳሹ አመክሮ ታስቦለት ከእስር ይወጣል የሚል ግምት መኖሩን የህግ አካላት ገልጸዋል። ይሁንና ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው እስከ አርብ ከሰዓት በኋላ ድረስ ከእስር አለመለቀቁን ለመረዳት ተችሏል። ...
Read More »የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ለግብርና ዘርፍ ለስራ ማስኬጃ የሚሰጠውን ብድር አቋረጠ
ኢሳት (ግንቦት 18 ፥ 2009) በቅርቡ ለግል የልማት ፕሮጄክቶች ሲሰጥ የቆየውን ብድር ያቋረጠው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ለግብርና ዘርፍ ለስራ ማስኬጃ የሚሰጠውን ብድር አቋረጠ። ባንኩ የወሰደው ይኸው ተጨማሪ ዕርምጃ በተያዘው የክረምት ወር ብድርን ወስደው በግብርና ምርት ላይ ሲሰማሩ ለነበሩ ባለሃብቶች ያልታሰበ ድንጋጤ ማሳደሩን ካፒታል የተሰኘ የቢዝነስ ጋዜጣ ዘግቧል። የብሄራዊ ባንክ ከቀናት በፊት ተግባራዊ ያደረገው ይኸው መመሪያ የብድር ጥያቄያቸው ተቀባይነት አግኝቶ ገንዘብ ...
Read More »ከኢሬቻ በዓል አከባበር ጋር በተያያዘ ግጭት አነሳስተዋል የተባሉ ሁለት ግለሰቦች ክስ ቀረበባቸው
ኢሳት (ግንቦት 18 ፥ 2009) ከሳሽ አቃቤ ህግ ባለፈው አመት ከኢሬቻ በዓል አከባበር ወቅት ጋር በተያያዘ ተከስቶ የነበረውን ግጭት አነሳስተዋል ያላቸውን ሁለት ግለሰቦች በሽብር ወንጀል መክሰሱ ታውቋል። ተከሳሾቹ ተፋ መልካ እና ከድር በዳሱ የተባሉ ግለሰቦች ሲሆን፣ በበዓሉ አከባበር ወቅት ከሃገር ሽማግሌዎች ድምፅ ማጉያን በመቀማትና ሁከት በማነሳሳት ለ55 ሰዎች ሞት ምክንያት ሆነዋል ተብለዋል። ከሳሽ አቃቤ ህግ ሁለቱን ተከሳሾች የሽብር ወንጀል ድርጊት ...
Read More »በጎዴ አንድ የአይር ሃይል ባልደረባ በርካታ መኮንኖችን ገድሎ ራሱን ማጥፋቱ ተሰማ
ግንቦት ፲፰ ( አሥራ ስምንት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት በኢትዮጵያና በሶማሊያ ድንበር በምትገኘው ጎዴ ከተማ የሰፈረው የመከላከያ ሰራዊት አባል የሆነው የጎንደር ተወላጅ ወታደር በርካታ መኮንኖችን ገድሎ በመጨረሻም ራሱን አጥፍቷል። ወታደሩ ድርጊቱን የፈጸመው በአየር ሃይል የምህንድስና ትምህርት ተምሮ ጎዴ በእግረኛ ወታደርነት መመደቡን ተከትሎ ነው። ምንጮች እንደገለጹት ፣ ወታደሩ ያለምንም ምክንያት ወደ ጎዴ ተወስዶ በእግረኛ ወታደር ...
Read More »ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው በ1 አመት ከስድስት ወር እስር ተቀጣ
ግንቦት ፲፰ ( አሥራ ስምንት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የፌደራል ከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የነገረ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራውን በአንድ አመት ከስድስት ወር እንዲቀጣ የወሰነበት ሲሆን፣ ጌታቸው የእስሩን ጊዜ የጨረሰ በመሆኑ፣ በሚቀጥለው ሳምንት ውስጥ ሊፈታ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል። ፍርድ ቤቱ ጋዜጠኛ ጌታቸው የወንጀለኛ መቅጫ አንቀጽ 257 ሀ እና መ ን በመተላለፍ ህዝቡን ለአመጽ ...
Read More »በአዳማ ከተማ የመኪና አደጋና የአስተዳደር ችግር ተባብሰው ቀጥሎአል
ግንቦት ፲፰ ( አሥራ ስምንት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በከተማዋ ውስጥ ያሉት ነባርና አዲስ የትራፊክ መብራቶች ከአምስት ዓመት እስከ ሁለት ዓመታት ድረስ አገልግሎት መስጠት ማቆማቸው ለትራፊክ አደጋዎች መበራከት ከፍተኛውን ድርሻ መውሰዱን ነዋሪዎች ይናገራሉ።የፈረስ ጋሪን ቦታ የተኩት ባጆች ለብቻ የሚጓዙበት መንገድ አለመሰራቱም ለመንገዶች መጨናነቅና ለተደጋጋሚ የመኪና አደጋ መከሰት ተጨማሪ ምክንያት ሆነዋል። ከተማዋ በየጊዜው ከንቲባዎችን ቀያይራለች። ከኅዳር 11 ቀን ...
Read More »ኢትዮጵያ ሰፊ የእርሻ መሬት ለሱዳን ለማስረከብ ዝግጅት መጨረሷ ታወቀ
ግንቦት ፲፯ ( አሥራ ሰባት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በቅርቡ በአካባቢ የሚንቀሳቀሱ ጸረ ሰላም ሃይሎችን እና ሰዎችን በህገወጥ መንገድ የሚያዘዋውሩትን ለመግታት በሚል በሁለቱ አገራት የጋራ ጦር የተቋቋመው ወታደራዊ እዝ፣ ሰፊ የሆነ የኢትዮጵያን ግዛት ለሱዳን ለማስረከብ እንቅስቃሴ ጀምሯል። የጋራ ጥምር ጦሩ በኢትዮጵያ አርሶአደሮች በኩል ሊቀርብ የሚችለውን ማንኛውንም ተቃውሞ ለመጨፍለቅ በዝግጅት ላይ ነው። ሰሞኑን የእርሻ መሬቱን ለማስረከብ እንቅስቃሴ መጀመሩን ...
Read More »ምስራቅ እዝን ለአመታት የመራውና በከፍተኛ ሙስናና ወንጀል የሚከሰሰው ጄኔራል አብረሃ በሌላ በሙስና በተዘፈቀ አዛዥ ተተካ
ግንቦት ፲፯ ( አሥራ ሰባት ) ቀን ፳፻፱ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የኢሳት የአካባቢው ወኪላችን እንደገለጸው በሶማሊ ክልል ለተፈጸመው ከፍተኛ እልቂት ተጠያቂ የሆነውና ከሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት ጋር ከፍተኛ የሙስና ትስስር እንዳለው የሚነገርለት ጄ/ል አብረሃ ወይም በቅጽል ስሙ ኳርተር፣ በሌላው በሙስና በተዘፈቀው ጄኔራል ማሹ በየነ መተካቱ ታውቋል። ጄ/ል አብርሃ ከምስራቅ እዝ ሃላፊነት ተነስቶ የመከላከያ የዘመቻ መምሪያ ሃላፊ ሆኖ ተሹሟል። ጄ/ል ሳሞራ ...
Read More »