.የኢሳት አማርኛ ዜና

በመተማ ከተማ የቦምብ ጥቃት ተፈጸመ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 16/2010) በሰሜን ጎንደር ዞን መተማ ከተማ የቦምብ ጥቃት ተፈጸመ። ትላንት ምሽት በተፈጸመው በዚሁ ጥቃት የህወሃት አባል በሆነ ግለሰብ ሆቴል ላይም ጉዳት መደረሱን ለማወቅ ተችሏል። በሆቴሉ የህወሃት አገዛዝ የቀጠናው የደህንነት ሃላፊዎች ስብሰባ ያደርጉ ነበር ተብሏል። በተፈጸመው ጥቃት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የከተማዋ ሁለት ባለስልጣናት ወደ ጎንደር ሆስፒታል መወሰዳቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ባልታወቁ ሃይሎች የተፈጸመውን ይህን ጥቃት በተመለከተ በመንግስት በኩል የተባለ ...

Read More »

በወልቂጤ ህዝባዊ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 10/2010) በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ህዝባዊ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ። በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች ላይ ዛሬ የተካሄደው ተቃውሞ በሰላማዊ መንገድ ቢጀመርም ልዩ ሃይል ሰዎችን ማሰሩን ተከትሎ ወደ ግጭት መቀየሩን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። በወልቂጤ ከተማ ሊገነባ የመሰረት ድንጋይ የተጣለለት ሆስፒታል ፕሮጀክት ወደ ትግራይ ተወስዷል የሚል መረጃ ህዝቡ ዘንድ መድረሱ ለተቃውሞው መቀስቀስ ምክንያት እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። ከአዲስ አበባ በ150 ኪሎ ሜትር ትርቃለች። ወደ ...

Read More »

የሃይማኖት አባቶች አወገዙ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 15/2010) በወልዲያ የተፈጸመውን ጭፍጨፋ የሃይማኖት አባቶች አወገዙት። በውጭ የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በሀገር ቤት የሚገኘው ቤተክህነት በጉዳዩ ላይ ዝምታን መመረጡ እጅግ እንዳሳዘናት በመግለጽ መግለጫ አውጥታለች። የፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን ኢማም ሼህ ካሊድ ኡመር የከፋ እልቂት ከመከሰቱ በፊት በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ሰከን እንዲል ጥሪ አድርገዋል። የኢትዮጵያ ተነሺ አብሪ መስራች ወንጌላዊ ዳንዔል ጣሰው ግድያውን የፈጸሙ ለፍርድ እንዲቀርቡ ...

Read More »

ኬንያ ወደ ጠፈር ሳተላይት ልታመጥቅ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 15/2010) ኬንያ ወደ ጠፈር ሳተላይት ለማምጠቅ ዝግጅት መጀመሯ ታወቀ። የኢትዮጵያ ጎረቤት የሆነችው ኬንያ በመጪው መጋቢት ወር የምታመጥቀው ይህ ሳተላይት የባህር ዳርቻዎቿን ለማሰስና የግብርና ስራዎቿን ለማገዝ እንደሚጠቅማትም ይፋ ሆኗል። ከአፍሪካ ሃገራት 8ኛ በመሆን ሳተላይት የምታመጥቀው ኬንያ የጃፓን የህዋ ምርምር ማዕከል የሙያ ምክር እንዲሁም በጃፓን መንግስት የ1 ሚሊየን ዶላር ድጋፍ ተደርጎለታል። ነገር ግን ይሄ ድጋፍ ቢደረግለትም ሳተላይቱን ሙሉ በሙሉ ሰርተው ...

Read More »

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ 3 እጩዎች ለትምህርት ሚኒስቴር አስተላለፈ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 15/2010) የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አመራር ቦርድ የሕወሃቱን እጩ ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሃና ካህሳይን ጨምሮ 3 እጩዎችን ለትምህርት ሚኒስቴር አስተላለፈ። ለአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንትነት በኦሕዴድ ከታጩት ፕሮፌሰር በቀለ ጉተማ ጀቤሳ በተጨማሪ ዶክተር ጄይሉ ኡመር ሁሴንም በእጩዎች ውስጥ ተካተዋል። ለዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንትነት ሕወሃትና ኦህዴድ መፋጠጣቸውን የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንትን ለመምረጥ ብቃትን መሰረት ባደረገ መልኩ ውድድር እየተካሄደ መሆኑ ሲገለጽ ቆይቷል። ...

Read More »

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ባለስልጣንን የሚመሩት የሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ አባላት ናቸው

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 15/2010) የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ባለስልጣን የሚባለውንና ለመገናኛ ብዙሃን ፈቃድ የሚሰጠውን ተቋም ሙሉ በሙሉ የሚመሩት የሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ አባላት መሆናቸው ተጋለጠ። የሕወሃትን ቀውስ ተከትሎ እየተበተነ ያለው መረጃ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሚሰሩ እንዲሁም በግል መገናኛ ብዙሃን የሚሳተፉ የሕወሃት አባላት ዝርዝርም ይፋ ሆኗል። በኢትዮጵያ በግል እንዲሁም በማህበረሰብ ለሚሰሩ ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንዲሁም የሕትመት ሚዲያዎች ፈቃድ የሚሰጠው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ባለስልጣን የተባለውን ተቋም የሚመሩት ...

Read More »

የወልድያውን ጅምላ ግድያ የተባበሩት መንግስታት አወገዘ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 15/2010) በወልዲያ በቃና ዘገሊላ በአል ላይ በወጡ ሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈጸመውን ጅምላ ግድያ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን አወገዘ። ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ እንዳለው በመንግስት ታጣቂዎች የተፈጸመው ጅምላ ግድያ ገለልተኛ በሆነ አካል በአስቸኳይ ተጣርቶ ጥቃት ፈጻሚዎቹ ተጠያቂ መሆን ይኖርባቸዋል። ጥቃቱን የሚፈጽሙ ያልሰለጠኑ የጸጥታ አካላትም ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ አገልግሎት እንዲሰጡ ትምህርት ሊሰጣቸው ይገባል ብሏል። የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን የወልዲያው ...

Read More »

በወልዲያ ህዝባዊ ተቃውሞው እንደቀጠለ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 15/2010) በወልዲያ የተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ ዛሬም ቀጥሎ መዋሉ ታወቀ።   በዕለቱ ይውል የነበረው የማክሰኞ ገበያም እንዳይቆም ተደርጓል። የተገደሉት ሰዎች ቁጥ እያሻቀበ ነው። በአልሞ ተኳሽ ከተመቱት ሌላ በስልት ተወግተው ሆስፒታል የገቡ በርካታ ሰዎችም እንዳሉ ይነገራል። የግጭቱ መንስዔ በበዓሉ ላይ የተለየ የፖለቲካ አመለካከት የሚያንጸባርቁ ወጣቶች እንደሆኑ በህወሃት አገዛዝ በኩል ተገልጿል። ለኢሳት ዛሬ በደረሰው መረጃ ግን ከ13 ሰዎች በላይ በግፍ ለተገደሉበት ...

Read More »

ጆርጅ ዊሃ የላይቤሪያን የመሪነት መንበር ተረከበ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 14/2010) ታዋቂው የእግር ኳስ ተጫዋች ጆርጅ ዊሃ ዛሬ የላይቤሪያን የመሪነት መንበር ተረከበ። በሞኖሮቪያ ሳሙኤል ዶ ስታዲየም በተካሄደው ደማቅ ስነስርዓት የላይቤሪያን የፕሬዝዳንትነት ስልጣን የተረከበው ጆርጅ ዊሃ ለተሰበሰበው ሕዝብ ባደርገው ንግግር ብቻዬን የማደርገው ነገር የለምና አግዙኝ አብራችሁኝ ሁኑ ሲል ጥሪ አቅርቧል። ላለፉት 12 አመታት በላይቤሪያ የመሪነት ስልጣን ላይ የቆዩትን ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍን ተክቶ የላይቤሪያ ፕሬዝዳንት በመሆን ዛሬ ቃለ መሃላ በመፈጸም ...

Read More »

ሁለት ድጋፍ ሰጪ አካላት በጋራ ለመስራት ተስማሙ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 14/2010) የመላው አማራ ሕዝብ ድርጅት /መኢሕድ/ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪና የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ የድጋፍ ትብብር በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ። የሁለቱ ድጋፍ ሰጭ የስራ አመራር አባላት በቨርጂኒያ ሒልተን ሆቴል ባደረጉት የስምምነት ስነ ስርአት ላይ እንደተገለጸው ፓርቲዎቹ የሕወሃትን ስርአት ለመለወጥ በጋራ ለመስራት ይተባበራሉ። በዚሁም የዲፕሎማሲ ጥረቶችን በጋራ ለማከናወን በአገዛዙ ላይ የሚካሄዱ ተቃውሞዎችን በትብብር ማካሄድና ጥቃት በአንደኛው ማህበረሰብ ...

Read More »