ፖሊሶች በአበል ጉዳይ እየተወዛገቡ ነው

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዳግማዊ ሚኒልክና በሌሎችም አካባቢዎች የሚሰለጥኑ ፖሊሶች በቀን የሚታሰብላቸው ገንዘብ በቂ ባለመሆኑ

ጥያቄ አንስተዋል። ፖሊሶቹ ለቁርስና ምሳ እንዲሁም ለሻሂና ቡና 24 ብር በቀን የሚታሰብላቸው ቢሆንም፣ ገንዘቡ አይበቃንም በሚል ጥያቄ አንስተዋል።

ፖሊሶቹ  ስልጣናውን ሳያቋርጡ ጥያቄያቸውን እንዲያቀርቡ የኮሚሽኑ ከፍተኛ ባለስልጣኖች ለማግባባት እየሞከሩ ነው።

በዳግማዊ ሚኒሊክ ት/ቤት ውስጥ ካለፉት 2 ሳምንታት ጀምሮ ከ500 በላይ ፖሊሶች እየሰለጡ ነው። ስልጣናው መጪውን ምርጫ ታሳቢ አድርጎ የሚሰጥ

ነው። በኮልፌ በነበረው  ስልጠና ላይ ፖሊሶች ከመብት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን አንስተው እንደነበር መዘገባችን ይታወቃል።