በአንዋር መስጊድ ከተፈጠረው ግጭት ጋር በተያያዘ የታሰሩ ሙስሊሞች በድጋሜ ተቀጠሩ

ነሃሴ ፯(ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ በአንዋር መስጊድ የተፈጠረውን ተቃውሞ መርተዋል በሚል ከታሰሩት መካከል 6 ሙስሊም

ኢትዮጵያውያን የዋስትና መብታቸውን ተነጥቀው ለሰኞ ችሎት እንዲቀርቡ ታዘዋል። በሌላ በኩል ደግሞ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የታሰሩት የሰማያዊ

ፓርቲ አባሏ ወ/ት ወይንሸት ሞላ ፣ የፎቶ ጋዜጠኛ አዚዛ ሙሃመድ እና ኢብራሂም አብዱልሰላም በ5 ሺ ብር  ዋስ እንዲለቀቁ ፍርድ ቤት በድጋሜ

አዟል። እስረኞቹ ቀደም ብሎ እንዲለቀቁ ትእዛዝ ተሰጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ ፖሊስ በሌላ ችሎት የጊዜ ቀጠሮ አስይዞባቸው ወደ እስር ቤት እንዲመለሱ

ተደርጓል። ይሁን እንጅ እሰረ ዳኞች ስብሰባ ላይ ናቸው በሚል ምክንያት እስረኞቹ ሳይፈቱ ማደራቸውን ለማወቅ ተችሎአል።