የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ኢሳት ወደ ኢትዮጵያ የሙከራ ስርጭት ጀመረ

መስከረም ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በገዢው ፓርቲ አፈና ከአንድ አመት በላይ ለሚሆን ጊዜ ታፍኖ ቆየው ኢሳት ወደ ኢትዮጵያ የሚያስተላልፈውን የሙከራ ስርጭት  ጀምሯል።

ከኒው ሆርን ቴሌቪዥን የአየር ስርጭት በመግዛት በሚቀጥሉት ቀናት ሙሉ ስርጭቱን የሚጀምረው ኢሳት፣ በቅርቡ ተጨማሪ የራሱ ሙሉ የስርጭት ጊዜ ይኖረዋል።

አዲሱ ስርጭት በኤ ቢ 7 በ7 ዲግሪ ዌስት ላይ በ 10815 ሜጋ ሀርዝ፣ በ27 ሺ 500 ሜትር ባንድ ሲምቦል ሬት፣ በ5 ስድስተኛ ኤፍ ሲ ይተላለፋል። ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ናይል ሳትን በመክፈት ስርጭቱን በቀላሉ ለማግኘት ይችላል።

ተጨማሪ መግለጫዎችን ሙሉ ስርጭቱ እንደተጀመረ እንሰጣለን።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide