የአልሸባብ ተዋጊዮች ኪስማዮን ለቀው ወጡ

መስከረም ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-የሶማሊያ መንግስትና በአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ስም የዘመተው የኬንያ ጦር በጋር በመሆን በአልሸባብ ላይ የከፈቱት ዘመቻ ወደ ፍጻሜው እየተቃረበ መምጣቱን መረጃዎች ያመለክታሉ።

አልሸባብ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ገቢ የሚያስገኝለትን የወደብ ከተማ የሆነችውን ኪስማዩን ለመልቀቅ መገደዱ፣ የድርጅቱን ፍጻሜ ሊያቃርበው እንደሚችል ነው ዘገባዎች የሚያመለክቱት።

የሶማሊያ ጦር አዛዥ እንደተናገሩት አልሸባብ ኪስማዩን ለቆ ቢወጣም ፣ የአፍሪካ ህብረት ጦር ግን ከተማዋን ገና ሙሉ በሙሉ አልተቆጣጠራትም።

የአልሸባብ ቃል አቀባይ የሆኑት አሊ ሙሀመድ ራጂ ” አልሸባብ ስልታዊ ማፈግፈግ ማድረጉን” አምነዋል።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide