በመተማ ከአቶ መለስ ሞት ጋር በተያያዘ ከ120 በላይ ሰዎች ታሰሩ

መስከረም ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ኢሳት እንዳረጋገጠው በአማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ዞን በመተማ ከተማ በአቶ መለስ ዜናዊ ሞት ደስታችሁን ገልጣችሁዋል የተባሉ ከ120 በላይ ሰዎች ታስረው ስቃይ እየደረሰባቸው ነው።

የመተማ አካባቢ ነዋሪዎች   እንደገለጡት አቶ መለስ ዜናዊ ሞታቸው እንደተሰማ ” መለስ እንኳንም ሞተ፣ ተገላገልን” በማለት በመጠጥ ቤቶች ውስጥም ሆነ በተለያዩ ቦታዎች ደስታቸውን ገልጠዋል የተባሉ ከ120 በላይ ሰዎች ታስረዋል።

ግለሰቦቹ ታስረው ከፍተኛ የሆነ ድብደባ እና ስቃይ እየደረሰባቸው መሆኑን የጠቀሱት ነዋሪዎች ፣ እስረኞቹ እስካሁን ድረስ ፍርድ ቤት አለመቅረባቸውም ታውቋል።

በዚሁ ዞን በጃን አሞራ ወረዳ ውስጥ የሚኖረው የኢህአዴግ አባልና ባለስልጣን የሆነው አቶ ዳምጠው ሞገስ ለኢሳት እንደተናገረው፡ ኢህአዴግ በእያንዳንዱ ቀበሌ ከ200 እስከ 400 የሚደርሱ አባሎች ወደ ወረዳና _ ወደ ዞን በመሄድ ሀዘናቸውን እንዲገልጡ  መመሪያ አውርዶ ነበር።

የአካባቢውን ህዝብ አስተባብሮ ለአቶ መለስ ዜናዊ  ሀዘናቸውን እንዲገልጡ ሃላፊነት ተሰጥቶት የነበረው ወጣት በጉዳዩ ዙሪያ ከኢሳት ጋር ቃለምልልስ አድርጓል።

የተሻለ ለቅሶ ለማሳየት ወይም ከሌሎች ወረዳዎች አንሶ ላለመገኘት ወረዳዎች ፉክክር ውስጥ ገብተው እንደነበር አስተባባሪው ገልጧል

ዋናዉ ተፈላጊዉ ነገር ወረዳዎች ሀዘናቸውን በበቂ ሁኔታ አልገለጡም ተብለው እንዳይገመገሙ ነበር ያለው አስተባባሪው፣ እርሱ እና ባልደረባው “አባይን የደፈረ መሪ ፣ ለራሱ ያልኖረ መሪ” የሚሉ ከዞን ተዘጋጅተው የመጡ መፈክሮችን ማሰማታቸውን ገልጧል

ለሀዘን የወጣው ህዝብ ሀዘኑን ገልጦ ሲጨርስ ከ64 ብር እስከ 700 ብር የሚደርስ ገንዘብ መቀበሉንና እርሱም እንደ ወረዳ ካቢኔ አባላት ሁሉ ከፍተኛው ተከፋይ እንደነበር  የተቀሰው አሰተባባሪው: በአበል ክፍያ የተነሳም ውዝግብ ተፈጥሮ እንደነበር አጋልጧል

ከአቶ ዳምጠው ሞገስ ጋር ያደረግነውን ሙሉ ቃለምልልስ በድረገጻችን ላይ መከታተል ትችላላችሁ።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide