በመንግስት እና በኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጭ ግንባር መካከል ድርድር ቢጀመርም፡ ጦርነቱም እንደ ቀጠለ ነው

መስከረም ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በመንግስት እና በኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጭ ግንባር መካከል  ድርድር ቢጀመርም፡ ጦርነቱም እንደ ቀጠለ ነው ሲሉ የግንባሩ ቃል አቀባይ ገለጡ

የኦብነግ ቃል አቀባይ  አቶ ሀሰን አብዱላሂ  በኬንያ አደራዳሪነት ተከታታይ የሆኑ ድርድሮችን ለማካሄድ ስምምነት ላይ ቢደረስም ፣ ጦርነቱ ግን አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን ተናግረዋል።

“እናንተ ከመንግስት ጋር ድርድር ውስጥ የገባችሁት ሀይላችሁ እየተዳከመ በመምጣቱ ነውን?” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ሀሰን ሲመልሱ ፣ ድርጅታቸው ከመጀመሪያው ጀምሮ በድርድር እንደሚያምን ገልጠው ፣  ከመቼውም ጊዜ በላይ በጠንካራ ሁኔታ ላይ መሆኑንም ተናግረዋል

ድርጅታችሁ ብቻውን ወደ ድርድር ከመቅረብ ይልቅ ከሌሎች ተቃዋሚ ድርጅቶች ጋር በጋራ በመሆን ብትደራደሩ ይበልጥ ሀይል አይኖራችሁም ነበር ወይ? ተብለው የተጠየቁት ቍል አቀባዩ  ፣ ከተወሰኑ ተቃዋሚ ድርጅቶች ጋር አብረው እየሰሩ መሆናቸውን፤ ከቁሪዎቹ ድርጅቶች ጋር ግን አብሮ ለመስራት እየቸገራቸው መምጣቱን ገልጠዋል

የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጭ ግንባር ከመንግስት ጋር የሚያደርገውን ድርድር በሚቀጥሉት 2 ወራት ውስጥ በሶስተኛ አገር እንደሚያካሂድ የገለጡት ቃል አቀባዩ፣ የድርድሩን ነጥቦች ከመናገር ተቆጥበዋል።

ከአቶ ሀሰን አብዲላሂ ጋር የተደረገውን ሙሉ ቃለምልልስ በድረገጻችን ላይ መከታተል ትችላላችሁ።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide