የህዳሴው ግድብን ግብጽና ሱዳን ሊመሩት ይገባል ተባለ

ህዳር ፲፯ (አስራ  ሰባት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ኢትዮጵያ በመገንባት ላይ የምትገኘው የህዳሴ ግድብ የአባይ ተፋሰስ ሀገሮችን የአባይ ውሀ ድርሻ በጽኑ የሚጎዳ በመሆኑ የጋራ ስምምነት ላይ ሊደርስ ይገባል ሲሉ አንድ የፖለቲካ ምሁር ገለጹ።

ግድቡ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ የአባይን ወንዝ ውሀ 86 በመቶ በመቆጣጠር በአባይ ላይ የበላይነቱን ትይዛለችና፤ በተለይ ግብጽና ሱዳን ከወዲሁ መፍትሄ ሊያበጁ ይገባል ብለዋል።

ኢትዮጵያ በበኩሏ ከህዳሴው ግድብ ግብጽና ሱዳን ይጠቀማሉ እንጂ የሚጎዳ ወገን የለም ስትል መከራከሯን ቀጥላለች ብሎል በሱዳን የሚታተመው ሱዳን ቪዥን ጋዜጣ።

በአለም አቀፉ የአፍሪካ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ የህዳሴው ግድብ በግብጽና በሱዳን ላይ ያለው ተጽኖ በሚል ረስ በተካሄደ ፎረም የተሳተፉት የፖለቲካ ምሁር ፕሮፌሰር ሀሰን አልፍሬ የህዳሴው ግድብ ፍትሀዊ የሚሆነው ግብጽና ሱዳን ተረክበው ስራውን ሲያከናውኑትና ግድቡን ሲመሩት ብቻ ነው ብለዋል።

እንደፕሮፌሰሩ ይህ ካልሆነ ኢትዮጵያ ብቻ ግድቡን መገንባት ቀጥላ ካጠናቀቀች በሆላ የአባይን ካርድ በግሏ ታስገባለች፤ 86 ከመቶ የአባይን ውሀ በመቆጣጠር። ይህ ደግሞ የሁለቱን ሀገሮች የአባይ ድርሻ በጽኑ ይጓዳል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ሌላው ምሁር በዚሁ ጉዳይ ላይ ደቡብ ሱዳንም ሌላ ስጋት እንደምትኋን ገልጸዋል፤ በተለይም የታላቁ አባይ ታላቅ ገባር የነጭ አባይ በርግዛቷ በመኖሩ ሲሉ ተናግረዋል። ስለዚህም የህዳሴው ግድብ የሚመለከታቸውን ያለማከረ አደገኛ ፕሮጀክት ነው ተብሎል።

የእትርሻ፣ የመስኖ ግድብ፣ የአካባቢ ጥበቃ፣ የኤሌክትሪክ ሀይል ባለርሙያዎችና ፖለቲከኞች እንደተሳተፉበት በተገለጸው በዚህ ፎረም የኢትዮጵያ የማእድንና የኢነርጂ ሚንስትር ኢትዮጵያ የግብጽና የሱዳንን ተጠቃሚነት የመገደብ የተደበቀ አጀንዳ የላትም ሲሉ አስተባብለዋል።