ኦብነግ ከመንግስት ሀይሎች ጋር መዋጋቱ ተዘገበ

፲፬( አስራ አራት )ቀን ፳፻፮ /  ኢሳት ዜና :- ኦጋዴን ፕሬስ እንደዘገበው የኦጋዴን ነጻ አውጭ ግንባር ከመከላከያ ሰራዊት እና ከልዩ ሚሊሺያዎች ጋር ባደረገው የተኩስ ልውውጥ 70 የኢትዮጵያ ወታደሮች እንደተገደሉ በእርሱ ወገንም የተወሰኑ ታጣቂዎች እንደሞቱ ገልጿል። እንደ ጋዜጣው ዘገባ 3  የመንግስት ወታደራዊ አዛዦችም ተገድለዋል። መንግስት አስተያየተቱን ባይሰጥም ልዩ ሚሊሺያ የሚባለው ሀይል የኦብነግን ወታደራዊ አዛዥ መግደሉን ለጋዜጣው እንደገለጹለት ተዘግቧል። በደጋሀቡር፣ ኮራሄና ፊክ ዞኖች በርካታ ሰዎች ተይዘው መታሰራቸውም ተዘግቧል።

በአካባቢው ስላለው ግጭት የአለማቀፍም የመገናኛ ብዙሀንም ሆነ የሲቪክ ድርጅቶች ተንቀሳቅሰው መዘገብ አይችሉም። በክልልሉ ውስጥ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየተፈጸመ መሆኑ ይታወቃል።

መንግስት በቅርቡ የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን በክልሉ ማክበሩ ይታወቃል።