ኢህአዴግ ምርጫውን አስታኮ ቤቶችን ለያከፋፍል ነው

ሰኔ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢህአዴግ መራሹ መንግሥት በቀጣይ ዓመት የሚጠናቀቀው የእድገትን የትራንስፎርሜሽን እቅድ በአብዛኛው ዘርፎች ባያሳካም የመጪውን ዓመት ምርጫ ተከትሎ በጊዜያዊነት የሕዝቡን ድጋፍ የሚያስገኙለትን ሥራዎች ለማከናውን አቅዶ መንቀሳቀስ መጀመሩን የውስጥ ምንጮች ገልጸዋል

በዚሁዕቅድመሠረትየመኖሪያቤትለማግኘትወደ 800ሺሕዝብየተመዘገበበትበአዲስ አበባከተማበያዝነውወርእናበነሐሴወር 40 ሺኮንዶምኒየምቤቶችንእጣለማውጣትናበዚህምድጋፍለማግኘትታቅዶአል፡፡

በተመሳሳይሁኔታእስከ ታህሳስወር 2007 ባሉትጊዜያትእንዲሁወደ 40ሺየሚሆኑተጨማሪቤቶችንለተጠቃሚዎችለማስተላለፍታቅዶእየተሰራመሆኑንምንጮቻችንጠቁመዋል፡፡

ከዚህቀደምየቤቶቹግንባታ 50 በመቶ እንኩዋን ሳይጠናቀቅ በአየር ላይ ዕጣ እንዲወጣ በማድረግ ዕድለኞች ቤታቸውን እስኪረከቡ እስከ ሁለት ዓመታት ጊዜ ይፈጅ የነበረው ጊዜ አሁን ከምርጫው ጋር በተገናኘ ዕጣው በወጣ ሰሞን ዕድለኞች ቤቱን እንዲረከቡ በከተማዋ አስተዳደር በኩል ጥንቃቄ እንዲደረግ በተሰጠው ማሳሰቢያ መሰረት ለመጀመሪያ ጊዜ እድለኞች እጣው በወጣበት ሰሞን ቤታቸውን ይረከባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በአዲስ አበባ ያለው መኖሪያ ቤት ችግር የኢህአዴግ አባላትም ጭምር በየጊዜው ቅሬታ የሚያቀርቡበትና የሚጋሩት በመሆኑ ገዥው ፓርቲ በጊዜያዊነት በሚወስዳቸው እርምጃዎች ጥገናዊ ለውጥ አገኝበታለሁ ብሎ ማመኑ ተጠቁሞአል፡፡

በተለይ በአስተኛና ጥቃቅን የተደራጁ ዜጎች ችግሮቻቸውን ማለትም የብድር፣የመስሪያ ቦታና የመሳሰሉት በአፋጣኝ ተፈትቶላቸው ይህን ኃይል የምርጫ ሠራዊት ለማድረግ መታሰቡም ታውቋል፡፡

ገዥው ፓርቲ ኢህአዴግ እጅግ የተለጠጠ የአምስት ዓመት ዕቅዱ በቀጣይ ዓመት መጨረሻ የሚጠናቀቅ ሲሆን በዚህ ዕቅድ መሠረት ይደረስበታል ተብሎ የታሰቡ ስራዎች በአብዛኛው ሳይሳኩ ቀርተዋል፡፡

በተለይባለፉትሁለትዓመታትበቡናላይየተመሰረተውኤክስፖርትመቀዛቀዙ መንግስትን ከፍተኛገቢአሳጥቶታል፡፡

የሰለጠነየሰውሃይልእጥረት፣የፋይናንስአቅምውስንነትእንዲሁምዕቅዱሁሉንምወገንአሳታፊባለመሆኑምክንያትከግብርናወደኢንዱስትሪይደረጋልየተባለውሽግግርበአየር ላይ መቅረቱን ምንጮች ይገልጻሉ፡፡

የግልባለሃብቱንበማሳተፍረገድየታየውዳተኝነትናበኢኮኖሚውስጥየመንግስትናበገዥውፓርቲስርያሉየንግድተቋማትጣልቃገብነትመጠናከርዕቅዱእንዳይሳካትልቅአስተዋጽኦማድረጋቸው ታውቋል፡፡

ኢህአዴግ በምርጫ የማሸነፊያ ስትራቴጂው መሰረት ለከተማ ነዋሪዎች መሬት በአነስተኛ ገንዘብ ያከፋፍላል። ለአርሶአደሮች ደግሞ የማዳበሪያ እና የምርጥ ዘር እዳ እፎይታ ይሰጣል።

ኢህአዴግ ይፋዊ ያልሆነ የምርጫ ቅስቀሳውን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን ፣ በተለያዩ ወረዳዎች በመንቀሳቀስ  በአምስት አመቱ ተገኙ ያላቸውን ድሎች በራሱ ካድሬዎች አማካኝነት ህዝቡ እንዲያውቃቸው እየጣረ ነው። በአንዳንድ አካባቢዎች ህዝቡ ኢህአዴግ ካሰበው በተቀራኒ እየተናገረ ሲሆን በቅርቡ በሳምንቱ መግቢያ በደብረብርሃን ከተማ ተካሂዶ በነበረው ውይይት ላይ ህዝቡ በልማቱ ተጠቃሚ አለመሆኑን መናገሩ ታውቋል።

በደብረብርሃን የነበረውን ስብሰባ ዜና እና የህዝቡን አስተያየት በነገው ዜና የምናቀርብ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።