ወንጀል ፈጽማችሁዋል ተብለው ለ3 ዓመታት የታሰሩ ወጣቶች ወንጀል ሰሪው ሲያዝ ተፈቱ

ሰኔ ፭(አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ ቄራ አካባቢ የሚኖሩ አለማየሁ ተክሌ፣ ታደሰ አበራ እና ተካልኝ ወልደማርያም በ2003 ዓም ሰኔ አካባቢ ቤት አቃጠላችሁ ተብለው ለ 1 አመት ያክል ከታሰሩ በሁዋላ፣ ድርጊቱን የፈጸመው ሰው ተይዞ ጥፋት መስራቱን ቢያምንም፣ ፖሊስ “አንዴ ተፈርዷል” በሚል ፍርዱን ጨርሰው እንዲወጡ በማስደረጉ፣ ከ3 አመታት በሁዋላ ከቂሊንጦ እስር ቤት መውጣታቸውን  ገልጸዋል።